0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበሱዳን ጎርፍ ግድብ ደርምሶ 30 ሰዎች ሞቱ“በምስራቅ ሱዳን ኅይለኛ ጎርፍ ውሃ ግድብ ደርምሶ ቢያንስ 20 መንደሮች ነዋሪ የሆኑ 30 ሰዎች መሞታቸው ተዘገበ፡፡ ይህም በርካታ ወራት ባስቆጠረው ጦርነት አብዝቶ የተጎዳውን አካባቢ የበለጠ አውድሞታል" ሲል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ትላንት ሰኞ መናገሩን አሶሴይትድ ፕሬስ ዘግቧል፣ ደረጀ ደስታ ወደ አማርኛ መልሶታል፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሠሩ የኮሜርሻል ኖሚኒስ ሠራተኞች ሊሰናበቱ ነውኮሜርሻል ኖሚኒስ ሓላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀጠራቸው በሺሕዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞች ሊሰናበቱ እንደኾነ ተገለጸ፡፡ ከሥራ ይሰናበታሉ የተባሉት ሠራተኞችም፣ ከነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የሥራ ውላቸው እንደሚቋረጥ ኮሜርሻል ኖሚኒስ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደሰጣቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ሠራተኞቹ፥ “ለረዥም ጊዜ ከሠራንበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ መብታችን ሳይከበር አላግባብ ከሥራ ልንወጣ አይገባም፤” ብለዋል፡፡...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በትግራይ ክልል ጉብኝት ላይ ናቸውበኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ፣ በትግራይ ክልል የሶስት ቀናት ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ ትላንት ሰኞ አመሻሹ ላይ መቀሌ የገቡት የአምሳደር ማሲንጋ ጉብኝት፣የፕሪቶሪያውን ስምምነት ውጤታማ አተገባበር በማረጋገጥ እና ፖለቲካዊ አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታትን አስፈላጊነት በማጉላት ላይ ያተኮረ መሆኑን በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አስታውቋል። አምባሳደሩ በዛሬው ውሏቸው፣ በኤምባሲው ድጋፍ ጥገና የተደረገለትንና...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ሞቃዲሾ ገቡሁለቱ ሃገሮች ካይሮ ላይ ወታደራዊ ስምምነት በተፈራረሙ ሁለት ሳምንታት እድሜ ሁለት የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ዛሬ ማክሰኞ ሞቃዲሾ ገብተዋል። ልዩ ልዩ የጦር መሳሪያዎችን የጫኑ እና ወታደራዊ መኮንኖችን ያሳፈሩት ሁለት ሲ-130 ወታደራዊ አውሮፕላኖች ከሞቃዲሾው አደን አዴ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መድረሳቸውን ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ሁለት የሶማሊያ ምንጮች አመልክተዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ መሀሙድ ባለፈው የነሃሴ ወር ካይሮ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMእስራኤል በሃማስ ተይዞ የቆየ ሌላ አንድ ታጋች አስለቀቅችሃማስ ባለፈው መስከረም ወር መገባደጂያ አስደንጋጭ ጥቃት ባደረሰበት ወቅት ተይዘው ከተወሰዱት ቁጥራቸው 250 የሚደርሱ ሰዎች መካከል የሆኑ አንድ ሌላ ታጋች ማስለቀቋን እስራኤል በዛሬው ዕለት አስታውቃለች። የ52 ዓመቱን ካይድ ፋርሃን አልካዲን አስረኛ ወሩን በያዘው የሁለቱ ወገኖች ጦርነት መሰንበቻውን ደቡባዊ ጋዛ ሰርጥ ውስጥ ባካሄደው ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ወቅት መታደጉን ያመለከተው የእስራኤል ጦር በአካባቢው ካለ አንድ የመተላለፊያ ዋሻ አቅራቢያ እንዳገኛቸው...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMቤጂንግ ላይ የቻይና እና የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት ይነጋገራሉየዩናይትድ ስቴትሱ ብሔራዊ የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ጄክ ሱሊቫን ከቻይናው ከፍተኛ ዲፕሎማት ዋንግ ዪ ጋር ዛሬ ቤጂንግ ላይ ተገናኝተው የሚያደርጉት ውይይት ‘ውጤታማ ይሆናል’ የሚል ተስፋ ማሳደራቸውን ተናገሩ። ዛሬ ከቀትር በኋላ ቤጂንግ የገቡት ሱሊቫን ከውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋንግ ጋር "ውጤታማ” ያሉትን ውይይት ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልጠዋል። "በምንስማማባቸውም ሆነ በሌሎችመጠነ ሠፊ ጉዳዮች ዙሪያ ልዩነቶቻችንን ተጨባጭ በሆነ መንገድ መመልከት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበቴላቪቭ ጎዳና ላይ በተፈጠረ ፀብ ሁለት ኤርትራውያን መገደላቸውን የእስራኤል ፖሊስ አስታወቀበኤርትራ ያለውን መንግስት በሚደግፉ እና በሚቃወሙ ኤርትራውያን መካከል የእስራኤል የንግድ ማዕከል በሆነችው ቴል አቪቭ ጎዳና ላይ ቅዳሜ እለት በተፈጠረ ጸብ ሁለት ኤርትራውያን መሞታቸውን የእስራኤል ፖሊስ አስታወቀ። ኤርትራዊያኑ ቴል አቪቭ ውስጥ በሚገኘው 'ሀግና' ጎዳና ላይ ድንጋይ በመወራወር ባካሄዱት ግጭት ስምንት ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸውም ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ጨምሮ ገልጿል። መግለጫው አክሎ፣ የሕክምና አካላትን እንደምንጭ በመጥቀስ "በግጭቱ ሁለት...0 Comments 0 Shares