ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሠሩ የኮሜርሻል ኖሚኒስ ሠራተኞች ሊሰናበቱ ነው
ኮሜርሻል ኖሚኒስ ሓላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀጠራቸው በሺሕዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞች ሊሰናበቱ እንደኾነ ተገለጸ፡፡
ከሥራ ይሰናበታሉ የተባሉት ሠራተኞችም፣ ከነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የሥራ ውላቸው እንደሚቋረጥ ኮሜርሻል ኖሚኒስ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደሰጣቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ሠራተኞቹ፥ “ለረዥም ጊዜ ከሠራንበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ መብታችን ሳይከበር አላግባብ ከሥራ ልንወጣ አይገባም፤” ብለዋል፡፡...