የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ሞቃዲሾ ገቡ
ሁለቱ ሃገሮች ካይሮ ላይ ወታደራዊ ስምምነት በተፈራረሙ ሁለት ሳምንታት እድሜ ሁለት የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ዛሬ ማክሰኞ ሞቃዲሾ ገብተዋል።
ልዩ ልዩ የጦር መሳሪያዎችን የጫኑ እና ወታደራዊ መኮንኖችን ያሳፈሩት ሁለት ሲ-130 ወታደራዊ አውሮፕላኖች ከሞቃዲሾው አደን አዴ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መድረሳቸውን ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ሁለት የሶማሊያ ምንጮች አመልክተዋል።
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ መሀሙድ ባለፈው የነሃሴ ወር ካይሮ...