0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMየሱዳን ወታደራዊ መንግስት ልዑካኖቹን ወደ ካይሮ እንደሚልክ አስታወቀየሱዳን ወታደራዊ መንግስት በካይሮ ከግብጽ እና አሜሪካ ሃላፊዎች ጋር እንዲወያዩ ልዑካኖቹን ነገ ሰኞ እንደሚልክ አስታውቋል፡፡ የ16 ወራት ጦርነትን ለማስቆም ያለመው የሰላም ድርድር የመሳተፍ ጥያቄን በተመለከተ ከዚህ ቀደም በጅዳ የተደረሰው ስምምነት ተግባራዊ እስካልተደረገ ድረስ በስዊዘርላንድ በሚደረገው የሰላም ድርድር ላይ እንደማይሳተፍ አስታውቋል፡፡ በአሜሪካ በተመራውና በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም ታልሞ በሲውዘርላንድ ጄኔቭ በተዘጋጀው ድርድር በጄኔራል...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበአቶ ጌታቸው ቡድን የተጠራ "ህወሓትን የማዳን" ስብሰባ በመቐለ ተካሔደለሁለት ከተከፈለው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ(ህወሓት) አመራር አንዱን ቡድን በሚመሩት የፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተጠራ “ህወሓትን የማዳን” የተባለ ስብሰባ፣ ዛሬ እሑድ፣ በመቐለ ከተማ ተካሒዷል። የአቶ ጌታቸው ቡድን፣ ዛሬ እሑድ፣ ነሐሴ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ስብሰባውን ያደረገው፣ በፓርቲው ሊቀ መንበር ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ቡድን፣ ባለፈው ማክሰኞ የጀመረውን ጉባኤ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMአዲሱ የቬትናም ፕሬዘዳንት በቻይና ጉብኝት እያደረጉ ነውበቅርቡ ወደ ስልጣን የመጡት የቬትናም ፕሬዘዳንት ቱ ላም የመጀመርያ የጉብኝት መዳረሻቸው ቻይናን አድረገዋል፡፡ ይህም ምንም እንኳን የደቡብ እስያዋ ሃገር ቬትናም ከአሜሪካና ሌሎች ሃገራት ጋር ያላትን ወዳጅነት እያሳደገች ቢሆንም ከጎረቤት ሃገሯ ቻይና ጋር ያላትን ግኑኝነት ቅድሚያ እንደምትሰጠው አመላካች ተደርጎ ተወስዷል፡፡ ፕሬዘዳንቱ በሆንግ ኮንግ አቅራቢያ የምትገኘው ዋና የማምረቻ እና የወጭ ምርት ማዕከል በሆነችው ጓንግዙ ግዛትን መጎብኘታቸውን የቻይና...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMማሊውያን ከአራት ዓመታት የወታደራዊ አገዛዝ በኋላም በኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ናቸውየማሊ ወታደራዊ ሁንታ የወቅቱን ፕሬዚደንት ከስልጣን አስወግደው ስልጣን ከያዙ ከአራት አመታት በኋላ የበዙ ማሊያውያን ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እየተባባሱ መምጣቱን እና የማያቋርጥ የኃይል መቆራረጥ የንግድ ድርጅቶቻቸውን እየጎዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምዕራብ አፍሪካዋ ሀገር እኤአ ነሀሴ 2020 በቀድሞ ቅኝ ገዥዋ ፈረንሳይ በሚደገፉ ሙሰኛ ገዥዎች፣ በተስፋፋው የጂሃዲስት ዓመፅ እና የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት የተቀሰቀሰውን የህዝብ ቁጣ ተከትሎ ነበር መፈንቅለ መንግስቱ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበአሜሪካ የአየር ላይ ትርዒት ተሳታፊዎች በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ሆስፒታል ገቡበአሜሪካ ኮሎራዶ በተካሄደው የአየር ላይ ትርዒት ተመልካቾች መካከል በአካባቢው በነበረው ከባድ ሙቀት ምክንያት አንድ መቶ የሚሆኑት አስቸኳይ ህክምና ሲፈልጉ አስር የሚሆኑት ደግሞ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ትላንት ቅዳሜ በተጀመረውና ዛሬም በሚቀጥለው “ ፓይክስ ፒክ ሪጅናል ኤር ሾው” በመባል የሚታወቀው ይህ ትርዒት በታዋቂው የዩናይትድ ስቴትስ የባህር ኃይል “ ሰማያዊ መላእክት” በሚል ስም የሚታወቁት የበረራ ኤግዚቢሽን ቡድን ትርኢት የሚያሳዩበት እና የተለያዩ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMእስራኤል ሁለት የሃማስ ከፍተኛ ታጣቂዎች መግደሏን አስታወቀችእስራኤል ትላንት ቅዳሜ በወሰደችው የአየር ጥቃት ሁለት የሃማስ ከፍተኛ ታጣቂዎች መግደሏን አስታውቃለች፡፡ እስራኤላውያንን በመግደል ተሳትፈዋል ያለቻቸው ከፍተኛ ታጣቂዎች በዌስት ባንክ ጄንኒን በተባለ ቦታ በመኪናቸው ውስጥ እንዳሉ መገደላቸውን ተገልጿል፡፡ የእስራኤል የደህንነት ተቋምና የመከላከያ ሃይሉ በጋራ ባወጡት መግለጫ የተገድሉት ታጣቂዎች አህመድ አቡ አራ እና ራፊት ዳዋሲ እንደሚባሉ አስታውቀዋል፡፡ እስራኤል በመግለጫዋ ሁለቱ ታጣቂዎች በዌስት ባንክ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMብሊንከን ወደ እስራኤል ይጓዛሉየዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አንተኒ ብሊንከን በጋዛ የተኩስ አቁም በሚደረግበት ጉዳይ ላይ ለመምከር ዛሬ እሁድ እስራኤል ይገባሉ ተብሎ ተጠብቋል፡፡ ይህ ጉዟቸውም በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ላለፉት 10 ወራት የዘለቀው ጦርነት እንዲያበቃ የሚያስችል የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ ዋሽንግተን እያደረገችው ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግፊት አካል እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ብሊንከን ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ወደ አካባቢው ያደረጉት አስረኛ ጉዟቸውም ዩናይትድ...0 Comments 0 Shares