ብሊንከን ወደ እስራኤል ይጓዛሉ
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አንተኒ ብሊንከን በጋዛ የተኩስ አቁም በሚደረግበት ጉዳይ ላይ ለመምከር ዛሬ እሁድ እስራኤል ይገባሉ ተብሎ ተጠብቋል፡፡
ይህ ጉዟቸውም በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ላለፉት 10 ወራት የዘለቀው ጦርነት እንዲያበቃ የሚያስችል የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ ዋሽንግተን እያደረገችው ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግፊት አካል እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ብሊንከን ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ወደ አካባቢው ያደረጉት አስረኛ ጉዟቸውም ዩናይትድ...