የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ
የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ፡፡ሚንስትሯ ዶ/ር ሒሩት ወ/ማርያም የመስሪያ ቤታቸውን የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንዳሉት የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚገነባው በአድዋ ከተማ ነው፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጋር በመተባበር የሙዚየሙን የግንባታ ፕሮጀክት መነሻ ጥናት አጠናቋል ተብሏል፡፡የአድዋ ከተማ አስተዳደር ለአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚሆን ቦታ ማዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡
ለግንባታው በአሜሪካ የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉልን ቃል ገብተዋል ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡በተያያዘ ከ13 አመት በፊት ከሮም የተመለሰውን እና በብረት ድጋፍ የቆመውን ቁጥር ሶስት የአክሱም ሐውልት የብረት ድጋፉን አንስቶ ለሐውልቶቹ ዘላቂ የመሰረት ጥገና ለማድረግ ከጣሊያን ድርጅት ጋር ውል መፈረሙን ሰምተናል፡፡
የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ እንዳሉት ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገባባቸውና የአለም ቅርስ ከሆኑ መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ሲሆን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ገጥመውታል፡፡መላ ለመፈለግም በኢትዮጵያ በቅርስ ጥገና ላይ የተሻለ እውቀት ያላቸው ምሁራን እንዲያጠኑት ተደርጓል ብለዋል፡፡
ቅርሱን ለመታደግ በመጪው ጊዜ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች የዩኔስኮ ፍቃድና ድጋፍ ለማረጋገጥ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ያሉት ሚንስትሯ በጀመርነው የጥር ወር አጋማሽ ከዩኔስኮ፣ አይኮምስ እና ኢክሮም ጥምር የቴክኒክ ኮሚቴ በላሊበላ በአካል ተገኝተው ስለ ጉዳዩ ለመምከር ቀጠሮ ተይዟል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን ሰማንያ ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያ የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ብትሆንም ብዙዎቹ እርጅና ተጭኗቸው የመፍረስ አደጋ እያንዣበበባቸው ነው ተብሏል፡፡
አገሪቱ እነዚህን ቅርሶች የሚጠግን የሰው ሀይል አለማፍራቷና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚመደበው በጀት ቅርሶቹን ለመጠገን በቂ አለመሆኑ ፈተና ሆኖብናል ብለዋል ዶ/ር ሒሩት፡፡የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው የሶስተኛ አመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የኤሌክትሮኒክስ ፊርማን ለመደንገግ እንዲሁም የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩን ለማቋቋም የቀረቡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ
የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ፡፡ሚንስትሯ ዶ/ር ሒሩት ወ/ማርያም የመስሪያ ቤታቸውን የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንዳሉት የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚገነባው በአድዋ ከተማ ነው፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጋር በመተባበር የሙዚየሙን የግንባታ ፕሮጀክት መነሻ ጥናት አጠናቋል ተብሏል፡፡የአድዋ ከተማ አስተዳደር ለአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚሆን ቦታ ማዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡
ለግንባታው በአሜሪካ የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉልን ቃል ገብተዋል ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡በተያያዘ ከ13 አመት በፊት ከሮም የተመለሰውን እና በብረት ድጋፍ የቆመውን ቁጥር ሶስት የአክሱም ሐውልት የብረት ድጋፉን አንስቶ ለሐውልቶቹ ዘላቂ የመሰረት ጥገና ለማድረግ ከጣሊያን ድርጅት ጋር ውል መፈረሙን ሰምተናል፡፡
የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ እንዳሉት ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገባባቸውና የአለም ቅርስ ከሆኑ መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ሲሆን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ገጥመውታል፡፡መላ ለመፈለግም በኢትዮጵያ በቅርስ ጥገና ላይ የተሻለ እውቀት ያላቸው ምሁራን እንዲያጠኑት ተደርጓል ብለዋል፡፡
ቅርሱን ለመታደግ በመጪው ጊዜ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች የዩኔስኮ ፍቃድና ድጋፍ ለማረጋገጥ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ያሉት ሚንስትሯ በጀመርነው የጥር ወር አጋማሽ ከዩኔስኮ፣ አይኮምስ እና ኢክሮም ጥምር የቴክኒክ ኮሚቴ በላሊበላ በአካል ተገኝተው ስለ ጉዳዩ ለመምከር ቀጠሮ ተይዟል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን ሰማንያ ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያ የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ብትሆንም ብዙዎቹ እርጅና ተጭኗቸው የመፍረስ አደጋ እያንዣበበባቸው ነው ተብሏል፡፡
አገሪቱ እነዚህን ቅርሶች የሚጠግን የሰው ሀይል አለማፍራቷና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚመደበው በጀት ቅርሶቹን ለመጠገን በቂ አለመሆኑ ፈተና ሆኖብናል ብለዋል ዶ/ር ሒሩት፡፡የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው የሶስተኛ አመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የኤሌክትሮኒክስ ፊርማን ለመደንገግ እንዲሁም የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩን ለማቋቋም የቀረቡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡