ረጲ የደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ግንባታ እስካሁን ድረስ ግን ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት አልጀመረም።

በአፍሪካ የመጀመሪያው ነው የተባለለት ረጲ የደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ግንባታው የተጀመረው ከአምስት ዓመት በፊት ነበር።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀ፥ ፕሮጀክቱ ሰኔ ወር 2009 ዓመተ ምህረት ነበር ግንባታው ተጠናቆ ስራ መጀመር የነበረበት ብለዋል።

የፕሮጀክቱ መጓተት ምክንያቶችን አስመልክተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ምስክር ነጋሽ እንደሚሉት፥ ወደ ግንባታው በሚገባበት ጊዜ በወቅቱ የኮንትራት ድርድር የተራዘመበት ሁኔታ መኖሩ በአንደኛነት አንስተዋል።

በሁለተኛ ደረጃም ከግንባታ ቦታ ላይ የነበሩ የአዲስ አበባ መስተዳድር ንብረቶች የሆኑ በወቅቱ ባለመነሳታቸው እነሱ እስኪነሱ ድረስ የወሰደው ጊዜ እንደነበር ተናግረዋል።

እንዲሁም ለማመንጫ የሚያገለግሉ እቃዎች ከውጭ አገር ተገዝተው የመጡ ከመሆናቸው አንፃር ግንባታው ስፍራ እስኪደርሱ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል ነው ያሉት።

እነዚህን እና ሌሎችንም መሰል ችግሮች አልፎ አሁን አፈጻጸሙ በመቶኛ ዘጠናዎቹ ውስጥ ገብቷል ከተባለ በኋላም ቢሆን በቅርቡ ይጠናቀቃል እየተባለ የ2010 ጥር ወር ላይ ደርሷል።

ከዚህስ በኋላ መቼ ነው ይህ የሀይል ማመንጫ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው ለሚለው ጣቢያችን ላነሳው ጥያቄ፥ “በጋራ የተነጋገርነው ጊዜው ሲደርስ እናሳውቃለን የሚል ነው” ሲሉ አቶ ምስክር ነግረዉናል።

ይህ ፕሮጀክት ግንባታው ከመጀመሩ በፊትም ቢሆን በጥናት ሶስት ዓመታትን አሳልፏል፤ በድምሩ ስምንት ዓመታት መሆኑ ነው።

ኢንጂነር አዜብ አስናቀ፥ ስራው ከ95 በመቶ የተጠናቀቀ ቢሆንም የተተከሉት ነገሮች በትክክል ይሰራሉ ወይስ አይሰሩም የሚለው ፍተሻ እና ሙከራ መደረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

ይሁን እንጂ በኮሪደሩ ውስጥ ነዋሪዎች እያሉ ሙከራ ለማድረግ የሚያስችል ሃይል መልቀቅ አይቻልም ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፥ ምክንያቱም አደጋ ሊያጋጥም ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።

የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው እንደሚሉት፥ አሁን ባለው መረጃ በመስመሩ ሁለት የልማት ተነሺዎች ብቻ የቀሩ ሲሆን እነዚህ ለማንሳት በፍጥነት እንፈፅመዋለን ብለዋል።

አቶ አባተ እንደሚናገሩት፥ የዚህ ፕሮጀክት መጠናቀቅ ምናልባትም ከሌሎቹም ባለድርሻ አካላት በላይ ከተማ አስተዳደሩ አጥብቆ ይፈልገዋል።

ምክንያቱም ፕሮጀክቱ ለመዲናዋ ፅዳት እና ውበት ትልቅ ፋይዳ ስላለው እኛ ሃላፊነት ወስደን በአጭር ጊዜ የልማት ተነሺዎች ጉዳይን እናስተካክላለን ብለዋል።

ፕሮጀክቱ እንደ ሃገር ከሚያመነጨው እና ወደ ብሄራዊ ቋት ከሚያስገባው ተጨማሪ የ50 ሜጋ ዋት ኃይል በላይ በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ለሚገኘው የከተማዋ ንፅህና የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ተብሏል።

ፕሮጀክቱ እንደተወራለት ከሆነ እጅግ ዘመናዊ በመሆኑ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ቀድሞ የደረቅ ቆሻሻ መጣያ የነበረው ስፍራ ሙሉ ለሙሉ ስለሚዘጋ በአካባቢው ነዋሪ ላይ ሲፈጥር የነበረውን መጥፎ ጠረን ያለው ጢስ እና ሽታ ማስቀረት ያስችላል።

አሁን ቆሻሻ የተከመረበት ቦታም ተስተካክሎ አፈር ከተሞላ በኋላ በአረንጓዴ ተክሎች ተሸፍኖ ወደ መናፈሻ ስፍራነት ይለወጣል።

ይህ ብቻ አይደለም፤ ቆሻሻው የኤሌክትሪክ ኃይል ካመነጨ በኋላ ተጨምቆ የሚወጣው ውኃ አትክልቶችን ለማልማት፣ በተረፈ ምርትነት የሚወጣው አመድም ለብሎኬት ማምረቻነት ይውላል።

አቶ አባተ እንደሚሉት እነዚህ እና መሰል ጥቅሞቹ ተደማምረው ነው ከተማ አስተዳደሩ የፕሮጀክቱን መጠናቀቅ ከሁሉም በላይ በጉጉት እንዲጠብቀው እና በባለቤትነት ስሜትም እንዲሰራ ያደረጉት።

ይሁን እና ምክትል ከንቲባው ፕሮጀክቱ ሲጀመር አካባቢ የካሳ ክፍያው ተጓቶ ስለነበር የልማት ተነሺዎችን በፍጥነት ከቦታው ከማንሳት ጋር በተያያዘ ችግሮች ነበሩ።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀም በበኩላቸው፥ የከተማ አስተዳደሩ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አንስተውልናል።

በአጠቃላይ ቦታው ከሰዎችና ከቤቶች ነጻ ከተደረገ በኋላም ቢሆን ምናልባትም ከከተማ አስተዳደሩ እውቅና ውጪ ብዙ አካባቢዎች ላይ እንደምናየው ዓይነት ቤቶችን ሰርተው በድጋሚ መኖር የጀመሩ ሰዎች ካሉ ከተማ አስተዳደሩ ማረጋገጥ እና አካባቢውን ነጻ ማድረግ ይጠበቅበታል።
ረጲ የደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ግንባታ እስካሁን ድረስ ግን ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት አልጀመረም። በአፍሪካ የመጀመሪያው ነው የተባለለት ረጲ የደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ግንባታው የተጀመረው ከአምስት ዓመት በፊት ነበር። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀ፥ ፕሮጀክቱ ሰኔ ወር 2009 ዓመተ ምህረት ነበር ግንባታው ተጠናቆ ስራ መጀመር የነበረበት ብለዋል። የፕሮጀክቱ መጓተት ምክንያቶችን አስመልክተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ምስክር ነጋሽ እንደሚሉት፥ ወደ ግንባታው በሚገባበት ጊዜ በወቅቱ የኮንትራት ድርድር የተራዘመበት ሁኔታ መኖሩ በአንደኛነት አንስተዋል። በሁለተኛ ደረጃም ከግንባታ ቦታ ላይ የነበሩ የአዲስ አበባ መስተዳድር ንብረቶች የሆኑ በወቅቱ ባለመነሳታቸው እነሱ እስኪነሱ ድረስ የወሰደው ጊዜ እንደነበር ተናግረዋል። እንዲሁም ለማመንጫ የሚያገለግሉ እቃዎች ከውጭ አገር ተገዝተው የመጡ ከመሆናቸው አንፃር ግንባታው ስፍራ እስኪደርሱ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል ነው ያሉት። እነዚህን እና ሌሎችንም መሰል ችግሮች አልፎ አሁን አፈጻጸሙ በመቶኛ ዘጠናዎቹ ውስጥ ገብቷል ከተባለ በኋላም ቢሆን በቅርቡ ይጠናቀቃል እየተባለ የ2010 ጥር ወር ላይ ደርሷል። ከዚህስ በኋላ መቼ ነው ይህ የሀይል ማመንጫ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው ለሚለው ጣቢያችን ላነሳው ጥያቄ፥ “በጋራ የተነጋገርነው ጊዜው ሲደርስ እናሳውቃለን የሚል ነው” ሲሉ አቶ ምስክር ነግረዉናል። ይህ ፕሮጀክት ግንባታው ከመጀመሩ በፊትም ቢሆን በጥናት ሶስት ዓመታትን አሳልፏል፤ በድምሩ ስምንት ዓመታት መሆኑ ነው። ኢንጂነር አዜብ አስናቀ፥ ስራው ከ95 በመቶ የተጠናቀቀ ቢሆንም የተተከሉት ነገሮች በትክክል ይሰራሉ ወይስ አይሰሩም የሚለው ፍተሻ እና ሙከራ መደረግ ያስፈልጋል ብለዋል። ይሁን እንጂ በኮሪደሩ ውስጥ ነዋሪዎች እያሉ ሙከራ ለማድረግ የሚያስችል ሃይል መልቀቅ አይቻልም ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፥ ምክንያቱም አደጋ ሊያጋጥም ይችላል ሲሉ አብራርተዋል። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው እንደሚሉት፥ አሁን ባለው መረጃ በመስመሩ ሁለት የልማት ተነሺዎች ብቻ የቀሩ ሲሆን እነዚህ ለማንሳት በፍጥነት እንፈፅመዋለን ብለዋል። አቶ አባተ እንደሚናገሩት፥ የዚህ ፕሮጀክት መጠናቀቅ ምናልባትም ከሌሎቹም ባለድርሻ አካላት በላይ ከተማ አስተዳደሩ አጥብቆ ይፈልገዋል። ምክንያቱም ፕሮጀክቱ ለመዲናዋ ፅዳት እና ውበት ትልቅ ፋይዳ ስላለው እኛ ሃላፊነት ወስደን በአጭር ጊዜ የልማት ተነሺዎች ጉዳይን እናስተካክላለን ብለዋል። ፕሮጀክቱ እንደ ሃገር ከሚያመነጨው እና ወደ ብሄራዊ ቋት ከሚያስገባው ተጨማሪ የ50 ሜጋ ዋት ኃይል በላይ በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ለሚገኘው የከተማዋ ንፅህና የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ተብሏል። ፕሮጀክቱ እንደተወራለት ከሆነ እጅግ ዘመናዊ በመሆኑ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ቀድሞ የደረቅ ቆሻሻ መጣያ የነበረው ስፍራ ሙሉ ለሙሉ ስለሚዘጋ በአካባቢው ነዋሪ ላይ ሲፈጥር የነበረውን መጥፎ ጠረን ያለው ጢስ እና ሽታ ማስቀረት ያስችላል። አሁን ቆሻሻ የተከመረበት ቦታም ተስተካክሎ አፈር ከተሞላ በኋላ በአረንጓዴ ተክሎች ተሸፍኖ ወደ መናፈሻ ስፍራነት ይለወጣል። ይህ ብቻ አይደለም፤ ቆሻሻው የኤሌክትሪክ ኃይል ካመነጨ በኋላ ተጨምቆ የሚወጣው ውኃ አትክልቶችን ለማልማት፣ በተረፈ ምርትነት የሚወጣው አመድም ለብሎኬት ማምረቻነት ይውላል። አቶ አባተ እንደሚሉት እነዚህ እና መሰል ጥቅሞቹ ተደማምረው ነው ከተማ አስተዳደሩ የፕሮጀክቱን መጠናቀቅ ከሁሉም በላይ በጉጉት እንዲጠብቀው እና በባለቤትነት ስሜትም እንዲሰራ ያደረጉት። ይሁን እና ምክትል ከንቲባው ፕሮጀክቱ ሲጀመር አካባቢ የካሳ ክፍያው ተጓቶ ስለነበር የልማት ተነሺዎችን በፍጥነት ከቦታው ከማንሳት ጋር በተያያዘ ችግሮች ነበሩ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀም በበኩላቸው፥ የከተማ አስተዳደሩ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አንስተውልናል። በአጠቃላይ ቦታው ከሰዎችና ከቤቶች ነጻ ከተደረገ በኋላም ቢሆን ምናልባትም ከከተማ አስተዳደሩ እውቅና ውጪ ብዙ አካባቢዎች ላይ እንደምናየው ዓይነት ቤቶችን ሰርተው በድጋሚ መኖር የጀመሩ ሰዎች ካሉ ከተማ አስተዳደሩ ማረጋገጥ እና አካባቢውን ነጻ ማድረግ ይጠበቅበታል።
Like
2
0 Comments 1 Shares