በአማራ እና ትግራይ ክልሎች በተያዘው ዓመት በጥናት በተለዩ 45 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ላይ የከርሰ ምድር ውሃ መገኛ አከባቢያዊ ካርታ ሊዘጋጅ መሆኑን የእርሻ እና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ዘንድሮ በጥናት በለያቸው በሁለቱ ክልሎች የመስኖ ከርሰ ምድር ውሃ፥ አርሶ አደሩን በመስኖ ልማት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው ተብሏል።

በሚኒስቴሩ አነስተኛ መስኖ ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ አወል ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖርት እንደተናገሩት፥ ሚኒስቴሩ የከርሰ ምድር ውሃ መገኛ አካባቢያዊ ካርታ ያዘጋጃል።

በ2010 ዓ.ም የተጠናቀቀው ይህ ጥናት፥ አቶ ኤልያስ በሁለቱ ክልሎች በ45 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃ 85 በመቶ መኖሩን አረጋግጧል ብለዋል።

በዚህ መልኩ የተለዩትን ቦታዎች ካርታ ከማዘጋጀት ጎን ለጎን በቁፋሮ ዘርፍ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን በማሰማራት ከየካቲት ወር ጀምሮ የቁፋሮ ስራ ይጀመራል ነው የተባለው።

ቁፋሮው ሲጠናቀቅ አርሶ አደሩ በሚወጣው የከርሰ ምድር ውሃ በመስኖ ልማቱ ተጠቃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
በአማራ እና ትግራይ ክልሎች በተያዘው ዓመት በጥናት በተለዩ 45 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ላይ የከርሰ ምድር ውሃ መገኛ አከባቢያዊ ካርታ ሊዘጋጅ መሆኑን የእርሻ እና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ዘንድሮ በጥናት በለያቸው በሁለቱ ክልሎች የመስኖ ከርሰ ምድር ውሃ፥ አርሶ አደሩን በመስኖ ልማት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው ተብሏል። በሚኒስቴሩ አነስተኛ መስኖ ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ አወል ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖርት እንደተናገሩት፥ ሚኒስቴሩ የከርሰ ምድር ውሃ መገኛ አካባቢያዊ ካርታ ያዘጋጃል። በ2010 ዓ.ም የተጠናቀቀው ይህ ጥናት፥ አቶ ኤልያስ በሁለቱ ክልሎች በ45 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃ 85 በመቶ መኖሩን አረጋግጧል ብለዋል። በዚህ መልኩ የተለዩትን ቦታዎች ካርታ ከማዘጋጀት ጎን ለጎን በቁፋሮ ዘርፍ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን በማሰማራት ከየካቲት ወር ጀምሮ የቁፋሮ ስራ ይጀመራል ነው የተባለው። ቁፋሮው ሲጠናቀቅ አርሶ አደሩ በሚወጣው የከርሰ ምድር ውሃ በመስኖ ልማቱ ተጠቃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
Like
2
0 Comments 1 Shares