Ethiopian Social Network Ethiopian Social Network
Search Results
See All Results
  • Join
    Sign In
    Sign Up
    Search

Directory

  • Users
  • Posts
  • Pages
  • Groups
  • Events
  • Blogs
  • Marketplace
  • Funding
  • Offers
  • Movies
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    በጦርነት የተጎዳችው የሱዳን ከተማ ኦምዱርማን
    በሱዳን በሕዝብ ብዛት ሁለተኛዋ ከተማ የሆነችው ኦምዱርማን፣ በአንድ ወቅት የደራ የገበያ ስፍራ ሆና እንዳልነበር፣ አሁን ለአንድ ዓመት ተኩል ያህል በዘለቀው ጦርነት ወድማለች ማለት ይቻላል። ቪኦኤ ብዙም ወደ ማትሞከረው ከተማዪቱ መግባት የቻለ ሲሆን፣ የቀድሞ ክብሯን የሚያስታውሱ ነዋሪዎችን አግኝቶ አነጋግሯል፡፡ ከአባይ ወንዝ ማዶ ተሻግራ ከምትገኘው ዋና ከተማዪቱ ካርቱም ጦርነቱ በተፋፋመበት ወቅት ሄንሪ ዊልከንስ ኦምዱርማን ተገኝቶ ተከታዩን ዘግቧል።
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    ባይደን አፍሪካን በተመለከተ በተመድ ጉባኤ ያሳዩት አቋም
    ፕሬዝደንት ጆ ባይደን፣ በአስተዳደራቸው ዘመን መጨረሻ፣ ፊታቸውን ወደ አፍሪካ አዙረዋል። በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በዓለም መሪዎች ፊት ሲናገሩ፣ የሱዳን ግጭት ትኩረት እንደሚሻ፣ ወደ አንጎላ እንደሚጓዙ እንዲሁም በፀጥታው ምክር ቤት ለአፍሪካ ሃገራት ሁለት መቀመጫ መሰተጡን እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። የቪኦኤ የዋይት ሃውስ ዘጋቢ አኒታ ፓወል ከኒው ዮርክ የላከችው ዘገባ ነው።
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    በጎሮ ዶላ ወረዳ ለዓመት የተቋረጠዉ ትምህርት ቢጀመርም 49 ትምህርት ቤቶች መውደማቸው ተነገረ
    የምስራቅ ቦረና ዞን መመስረትን ተከትሎ በተቀሰቀሰዉ ተቃውሞ በጎሮ ዶላ ወረዳ ላለፈው አንድ ዓመት ሙሉ ተቁዋርጦ የነበረው ትምህርት ዘንድሮ መጀመሩን ነዋሪዎች እና የወረዳው ባለሥልጣናት ተናግረዋል። የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ በአባ ገዳዎች ሽምግልና እንደተጀመረ የተነገረ ሲሆን፣ ያለፈው ዓመት ያለአገልግሎት የቆዩት 49 ትምህርት ቤቶች ከአገልግሎት ውጭ መሆናቸውን የወረዳው የትምህርት ፅህፈት ቤት ገልፆአል።
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አሳሳቢ ሆኖ መቀጠሉን ኢሰመኮ ገለፀ
    በኢትዮጵያ በግጭት አካባቢዎች የሚፈፀሙ ዘርፈ ብዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አሳሳቢ ሆነው መቀጠላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፣በግጭት ዐውድ ውስጥ ያሉ አካባቢዎችን የሩብ ዓመት የሰብዓዊ መብት ሁኔታ የተመለከተ ሪፖርት ትላንት አመሻሽ ላይ አውጥቷል፡፡ ሪፖርቱ፣ በአምስት ክልሎች ውስጥ በርካታ ሲቪሎች መገደላቸውን፣ ብዙዎች ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን እና ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱን አመልክቷል፡፡ በግጭት ተሳታፊ...
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    የመስቀል ደመራ በዓል ዛሬ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ተከብሯል
    የ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ስነስርዓቶች ተከብሯል። በአዲስ አበባ በደማቅ ሁኔታ የተካሄደውን የበዓሉን አከባበር የተከታተለው ዘገቢያችን ከአዲስ አበባ ነው።
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    የሱዳን የጦር ኃይል በካርቱም በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ይዞታዎች ላይ ጥቃት አደረሰ
    የሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ዛሬ ሐሙስ በአየር እና በመድፍ ጥቃቶች መናወጧን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ የአይን አማኞች እና ወታደራዊ ምንጮችን ጠቅሶ ዘገበ፡፡ የጦር ሠራዊቱ የፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ይዞታዎችን የደበደበ ሲሆን በርካታ ነዋሪዎች እንደገለጡት ግጭቱ ሌሊት ላይ ነው የጀመረው፡፡ የዛሬው ጥቃት የጦር ኃይሉ በዋና ከተማዋ በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቁጥጥር ሥር ያሉ ቦታዎችን ለመያዝ ከወራት በኋላ የሰነዘረው ከባድ ጥቃት እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ የዛሬው ጥቃት የደረሰው...
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    ወደፍሎሪዳ በከፍተኛ ፍጥነት በማምራት ላይ ያለችው ሃሪኬይን ሄለን ከባድ አደጋ ደቅናለች
    ከባድ ዝናብ ይዛ በሜክሲኮ ባህረ ሰላጤ በከፍተኛ ፍጥነት እየተጓዘች ያለችው ሃሪኬን ሄለን የዩናይትድ ስቴትስ ፍሎሪዳ ግዛት በማቅናት ላይ መሆኗን የዩናይትድ ስቴትስ ብሔራዊ የሃሪኬን ክትትል ማዕከል አስታወቀ፡፡ በአንድ አካባቢዎች እስከ ስድስት ሜትር ከፍታ ያለው ለሕይወት አደገኛ የሆነ ዝናብ ሊያስከትል እንደሚችል ማዕከሉ አመልክቷል፡፡ በሜክሲኮ ባሕረ ሰላጤ አድርጋ በሰዓት 155 ኪሎ ሜትር ፍጥነት ባለው ኅይለኛ አውሎ ንፋስ የምትውዘገዘገው ኽሪኬን ሄለን ዛሬ...
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • VOA - Amharic shared a link
    2024-09-27 08:34:02 -
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    79ኛው የመንግሥታቱ ድርጅት ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ
    79ኛው የመንግሥታቱ ድርጅት ጉባኤ ከተጀመረ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል፡፡ “ማንንም ወደኋላ ሳንተው ለሠላም ለዘላቂ ልማት እና ለሠብዓዊነት እድገት እንሰራለን” የሚል መሪ ቃል አንግቧል፡፡ በሁለተኛው ቀን ጉባኤ ላይ ሊቢያ፣ ላይቤሪያ፣ ናሚቢያ እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ንግግር ካደረጉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል ናቸው፡፡ የፈረንሳይ እና የዩክሬንም መሪዎችም በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት ንግግር አድርገዋል፡፡ የብዙዎችን ትኩረት የሳበ ንግግር ያደረጉት ፕሬዚደንት ዘለንስኪ የሩሲያ...
    0 Comments 0 Shares
    Please log in to like, share and comment!
  • Displaying (289081-289088 of 310342)
  • «
  • Prev
  • 36134
  • 36135
  • 36136
  • 36137
  • 36138
  • Next
  • »
© 2026 Ethiopian Social Network English
English Amharic
Contact Us Directory