የሱዳን የጦር ኃይል በካርቱም በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ይዞታዎች ላይ ጥቃት አደረሰ
የሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ዛሬ ሐሙስ በአየር እና በመድፍ ጥቃቶች መናወጧን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ የአይን አማኞች እና ወታደራዊ ምንጮችን ጠቅሶ ዘገበ፡፡ የጦር ሠራዊቱ የፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ይዞታዎችን የደበደበ ሲሆን በርካታ ነዋሪዎች እንደገለጡት ግጭቱ ሌሊት ላይ ነው የጀመረው፡፡ የዛሬው ጥቃት የጦር ኃይሉ በዋና ከተማዋ በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቁጥጥር ሥር ያሉ ቦታዎችን ለመያዝ ከወራት በኋላ የሰነዘረው ከባድ ጥቃት እንደሆነ ተመልክቷል፡፡
የዛሬው ጥቃት የደረሰው...