• AMHARIC.VOANEWS.COM
    ካመላ ሄሪስና ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ ምሽት ክርክር ይገጥማሉ
    ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሄሪስ እና የቀድሞው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ፊለደልፊያ ላይ የመጀመሪያ ክርክራቸውን ዛሬ ምሽት ያደርጋሉ። ተንታኞች እንደሚሉት፣ በዐቃቤ ሕግነት ዘመናቸው ጠንካራ ተሟጋች የነበሩት ካመላ፣ በአሜሪካ ፖለቲካ የመልስ ምት በመሰንዘር ከሚታወቁ ትራምፕ ጋራ በቃላት ልውውጥ የሚያደርጉት ፍልሚያ፣ የሃገሪቱ ፕሬዝደንት ለመሆን በሚያደርጉት ፉክክር ውጤት ሁነኛ ድርሻ ሊኖረው ይችላል። ሙሉ ዘገባውን ከተያይያዘው የድምጽ ማጫወቻ ይከታተሉ።
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ህወሓት ከኤርትራ መንግሥት ጋራ ንግግር ማካሄዱን ገለፀ
    የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ ፓርቲያቸው ከኤርትራ አመራሮች ጋራ ከስድስት ወራት በፊት ዱባይ ላይ ውይይት ማድረጉን፣ ሊቀመንበሩ ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ። በዚያ ውይይት ላይ ህወሓትን በመወከል የተሳተፉት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ መሆናቸውን የጠቀሱት ሊቀመንበሩ፣ ውይይቱ የተካሄደው "በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዕውቅና" ነው ብለዋል። ሊቀመንበሩ ዛሬ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ከአሜሪካ የተላኩት የመጀመሪያዎቹ የኤምፖክስ ክትባቶች ዴሞክራቲክ ኮንጎ ገብተዋል
    የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ባለሥልጣናት ከዩናይትድ ስቴትስ የተላኩት የኤምፖክስ 50 ሺህ ክትባቶች ከዩናይትድ ስቴትስ መግባታቸውን አስታውቀዋል፡፡ ዛሬ ማክሰኞ ከዩናይትድ ስቴትስ የተላኩት በቀድሞ ስሙ የዝንጀሮ ፈንጣጣ ክትባቶች ኮንጎ የደረሱት ከአውሮፓ ህብረት የተላኩት የመጀመሪያዎቹ ክትባቶች ከደረሱ ከአንድ ሳምንት በኋላ ነው። በበሽታው በጣም በተጎዱት ኤኩዊተር፥ ደቡባዊ ኪቩ እና ሳንኩሩ በተባሉት ሦስት አውራጃዎች የሚኖሩ አዋቂዎች ከመጭው የጎርጎርሳዊያኑ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ሂዩማን ራይትስ ዋች ሱዳን ላይ ጠንካራ የጦር መሣሪያ ማዕቀብ እንዲጣል ጠየቀ
    የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ወደ ሱዳን ምዕራብ ዳርፉር ግዛት የጦር መሣሪያ መላክን የሚከለክለው ማዕቀብ፤ መታደስ አለመታደስ ላይ ነገ ረቡዕ ድምጽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋሙ ሂዩማን ራይትስ ዋች ከነገው ድምጽ አሰጣጥ ቀደም ብሎ የጸጥታ ምክር ቤቱ በምዕራብ ዳርፉር ላይ የሚያተኩረውን የጦር መሣሪያ ማዕቀብ ሰፋ በማድረግ በመላ ሱዳን ሥራ ላይ እንዲያውለው አሳስቧል። የሱዳን መንግሥት ዕገዳውን ይቃወማል።...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በዋሽንግተን ዲሲ ሜዳ
    በኢትዮጵያ በርካታ የኳስ ደጋፊ ያላቸው አትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግርኳስ ክለቦች በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ኦዲ ፊልድ ስታድየም የወዳጅነት ጨዋታ አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ክለቦች በአሜሪካ ለመጀመርያ ጊዜ ባደረጉት በዚህ ጨዋታም ኢትዮጵያ ቡና 2 ለ1 ማሸነፍ ችሏል፡፡ ይህንና ሌሎች ስፖርታዊ መረጃዎችን ከተያያዘው ፋይል ይመልከቱ፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የኢትዮጵያ ዘመን ቀመር ለምን ተለየ?
    ኢትዮጵያ በየአመቱ መስከረም ወር ላይ አዲስ አመትን የምትቀበልበት የራሷ የዘመን አቆጣጠር ያላት ሃገር ናት:: አስራ ሶስተኛ ወር የምትባለው ጳጉሜ ወርን ጨምሮ በቀንና አመታት አቆጣጠርም ከአውሮፖውያ የዘመን ቀመር በተለየ ትቆጠራለች:: የአሜሪካ ድምጽ የ2017 ዓ.ም አዲስ አመት መቃረብን ምክንያት በማድረግ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ በርካታ መጽሃፍትን ያሳተሙትን የስነ ፈለክ ባለሙያ መጋቢ ሃዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰን አነጋግሯቸዋል:: የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ስለ አዲሱ ዓመት የተለያዩ ክልሎች ነዋሪዎች አስተያየት
    እየተሸኘ ያለው አዲስ ዓመት ምን ትቶ አልፏል መጭውስ ምን ተስፋ ሰንቋል? ለአዲሱ ዓመት “ሁሉም ሰው ሊመኘው የሚገባው ነገር ሰላም ብቻ ነው” ይላሉ በአማራ ክልል የባህርዳር ነዋሪዋ ወ/ሮ ወይንሸት ገመቹ፡፡ ከቤንሻንጉል ክልል የተፈናቀሉትና በሂደቱም ባለቤታቸውን በሞት ያጡት ወ/ሮ ወይንሸት ገመቹ አራት ልጆቻቸውን በህይወት ለማሰንበት እየተጣጣሩ መሆኑን ነግረውናል፡፡ ወ/ሮ ወይንሸት ስለመጭው ዓመት አዲስ ተስፋም ሆነ ውጥን ባይኖራቸውም አሮጌውን ዓመት...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    በሰሜን ጎንደር፣ ዳባት ከተማ አንድ ታጣቂ 2 ሰዎችን ገደለ
    በሰሜን ጎንደር ዞን፣ ዳባት ከተማ አንድ ታጣቂ ባለፈው አርብ ፈፀመው በተባለ ጥቃት፣ አንድ ኤርትራዊ ስደተኛን ጨምሮ፣ 2 ሰዎች መገደላቸውን፣ ስደተኞች ተናገሩ፡፡ በዛው ሳምንት፣ በዳባት ወረዳ፣ በአለምዋጭ መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ 2 ኤርትራውያን ስደተኞችም ታጣቂዎች ባደረሱባቸው ጥቃት ቆስለው ወደ ጎንደር ሆስፒታል መወሰዳቸውን፣ ስደተኞቹ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል፡፡ የመጠለያ ጣቢያው የሚገኝበት የዳባት ወረዳ፣ ጭላ ቀበሌ አስተዳደር በበኩሉ፣ በዳባት ከተማ ሁለት...
    0 Comments 0 Shares