0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMኮንጎ ውስጥ ከወህኒ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ ላይ 129 ሰዎች መገደላቸው ተሰማኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ውስጥ እስረኞች ከወህኒ ቤት ለማምለጥ ሲሞክሩ 129 ሰዎች መገደላቸው ተገለጠ። የመንግሥቱ ቃል አቀባይ በኤክስ ገጻቸው ላይ እንዳስታወቁት የጸጥታ ኅይሎች ትላንት ሰኞ ማለዳ በዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ከሚገኘው ከትልቁ ወህኒ ቤት እስረኞች ሰብረው ሊያመልጡ ሲሉ ከባድ ተኩስ ተነስቷል። የጸጥታ ኃይሎች የወህኒ ቤቱን አካባቢ አጥረውታል። ከወህኒ ቤቱ የወጡ ምስሎች 24 ሊያመልጡ የሞከሩ እስረኞች እጅግ ከተጨናነቀው የማካላ ማዕከላዊ እስር ቤት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMትራምፕ በሰማዕታት መቃብር ላይ ፎቶ መነሳታቸው ነቀፌታን አስከተለየቀድሞው ፕሬዝደንትና የሪፐብሊካን ፓርቲው ፕሬዝደንታዊ እጩ ዶናልድ ትረምፕ፣ አርሊንግተን በሚገኘው የሰማኅታት መቃብር ላይ ፎቶ መነሳታቸው ነቀፌታን ያስከተለ ሲሆን፣ አንዳንድ የሰማኅታቱ ቤተሰቦች ግን ድጋፋቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። የዲሞክራቲክ ፓርቲው ፕሬዝደንታዊ እጩ ካመላ ሄሪስም ድርጊቱን “ፖለቲካዊ ትኩረት ለማግኘት” የተደረገ ነው ሲሉ አውግዘዋል።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMግብፅ በሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ለተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ቅሬታ አቀረበችግብፅ ለምክር ቤቱ በጻፈችው ደብዳቤ “ሕልውናዬን እና የሕዝቦቼን ጥቅም ለማስከበር ሁሉንም እርምጃዎች ለመውሰድ ዝግጁ ነኝ” ብላለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የግድቡ ሁለት ተርባይኖች ከሳምንት በፊት ኃይል ማመንጨት መጀመራቸውን እና የግድቡ ግንባታም መገባደዱን መግለጻቸውን ተከትሎ ግብፅ ባሰማችው ቅሬታ፣ የኢትዮጵያ 'የአንድ ወገን እርምጃ' የቀጠናውን መረጋጋት አደጋ ላይ ይጥላል ብላለች፡፡ ይህንን አስመልክቶ ሞያዊ ትንታኔ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበደቡብ ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ክፍያ መቅረት እና ያስከተለው ቀውስበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ስለማይከፈላቸው አንዳንድ መምህራን የተማሩባቸውና ሲያገለግሉበት የነበረውን ሞያ ትተው በግብርና ሥራ መሰማራታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ:: በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ውስጥ በሚገኙ 21 ወረዳዎች ተቀጥረው በማገልገል ላይ የነበሩ የመንግሥት ሠራተኞች የወር ደሞዛቸው ለረዥም ጊዜ በመቁረጡ ለኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ችግሮች ተጋለጣቸውን አስረድተዋል:: በዳሞት ወይዴ ወረዳ ብቻ ከ3ሺህ በላይ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተማሪዎች የሚቀበልበትን አሰራር ሥራ ላይ ለማዋል ተዘጋጅቻለሁ አለየአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከመጪው 2017 የትምህርት አመት ጀምሮ፣ ተማሪዎችን የሚቀበልበትን አዲስ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን አስታወቀ፡፡ የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ፣ በዛሬው ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው የመንግስት ራስገዝ ከፍተኛ የትምሕርት ተቋም ከመሆኑ ጋር ተያይዞ፣ በመጪው አመት በዩኒቨርሲቲው የሚማሩ ተማሪዎች በመንግስት የሚመደቡ ሳይሆኑ፣ በተቋም መስፈርት መሰረት የሚመለመሉ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ጀምሮ ወደ አስመራ አልበርም አለየኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ማክሰኞ ጀምሮ የሚያቆም መሆኑን አስታወቀ። አየር መንገዱ ኤክስ በተሰኘው የማሕበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ከነገ ነሃሴ 28, 2016 ዓም ጀምሮ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ የሚያቋርጥ መሆኑን ለደንበኞቹ መግለጽ ይወዳል፤ ብሏል። አየር መንገዱ ወደዚያ የሚያደርጋቸውን በረራዎች ለማቋረጥ ለወሰደው ውሳኔ ኤርትራ ውስጥ ያጋጠመው ‘እጅግ አዳጋች’ ያለውን የሥራ ሁኔታ በምክኒያትነት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየስድስት እስራኤላውያን ታጋቾችን መገደል በእስራኤል በሺዎች ለተቃውሞ አደባባይ ወጡየስድስት እስራኤላዊያን ታጋቾች አስከሬኖች በደቡባዊ ጋዛ በሚገኝ በምድር ውስጥ ለውስጥ መተላለፊያ ዋሻ መገኘታቸውን ተከትሎ እስራኤላዊያን ድንጋጤ እና ቁጣቸውን መግለጻቸውን ቀጥለዋል። አንዳንዶቹም የሀገሪቱን መንግሥት ከሐማስ ጋር ቀደም ብሎ ከሐማስ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ ባለመቻል ወንጅለዋል። ዛሬ ሰኞ በትልቁ የእስራኤል የሠራተኛ ማሕበር የተጠራ አገር አቀፍ የሥራ ማቆም አድማ ተካሂዷል። ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።0 Comments 0 Shares