0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMአሜሪካ ቪየትናም የዩክሬንን ሉዓላዊነት እንድትደግፍ አሳሰበችየሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በሃኖይ ያደረጉትን የአንድ ቀን ጉብኝት ተከትሎ ቪየትናም የዩክሬንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንድትደግፍ ዩናይትድ ስቴትስ አሳሰበች። ፑቲን ወደ ቪየትናም የተጓዙት በሰሜን ኮሪያ የነበራቸውን የሁለት ቀናት ቆይታ ተከትሎ ሲሆን፣ እየተባባሰ የመጣውን የምዕራባውያን ማዕቀም ለመጋፈጥ የሚያስችላቸው ጥምረት ለመፍጠር በእስያ የሚያደርጉት ጉብኝት አካል ነው። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማቲው ሚለር...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበኬንያ በቀጠለው የተቃውሞ ጥሪ አንድ ሰው ተገደለበኬንያ ሊደረግ የታቀደውን የታክስ ጭማሪ በመቃወም ከተደረገው የወጣቶች ሰልፍ ጋራ በተያያዘ አንድ ሰው ተገድሏል፡፡ ፖሊሶችን የሚከታተለው ገለልተኛ ቡድን፣ ትላንት ኀሙስ የተካሔደውን ተቃውሞ ተከትሎ በናይሮቢ ሕይወቱ ያለፈው ግለሰብ፣ በፖሊስ ጥይት ተመትቶ እንደኾን እያጣራኹ ነው፤ ብሏል። ፖሊስ፣ ዛሬ ዐርብ እንዳስታወቀው፣ ተቃዋሚዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሔድ የተቃውሞ ሰልፍ ጠርተዋል፡፡ በኬንያ ወጣቶች መሪነት የተነሣሣውና ባለፈው...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMተመድ በኢራን ከሂጃብ ጋራ የተያያዙ የመብት ጥሰቶችንና የሞት ቅጣቶችን አወገዘየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዐዲስ ባወጣው ዘገባ፣ የኢራን መንግሥት፥ የሂጃብ ሕግን በሚጥሱ ሴቶች ላይ እየፈጸመ ያለውን ከፍተኛ ግድያ እና የኀይል ርምጃ አውግዟል፡፡ ዘገባው እንዳመለከተው፣ እ.ኤ.አ በ2023 ቢያንስ 834 ሰዎች ተገድለዋል። ይህም፣ ከቀደመው ዓመት ጋራ ሲነጻጸር 43 በመቶ ጨምሯል። ከአደገኛ ዕፆች ጋራ በተያያዙ ወንጀሎች የሚፈጸሙ ግድያዎች፣ በ84 በመቶ ከፍ ማለቱ ሲነገር፣ የአሁኑ በዐሥር ዓመታት ውስጥ ከፍተኛው ነው፤ ተብሏል።...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበሞጣ ቀራንዮ ከተማ ሰባት ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹበምሥራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ቀራኒዮ ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ የፋኖ ታጣቂዎች በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ተከትሎ፣ በደብረ ቀራኒዮ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ሰባት ሲቪሎች መገደላቸውን፣ የቤተ ክርስቲያኑ አገልጋይ እና በቦታው ነበርን ያሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ ሟቾቹ፣ ከዕለቱ አንድ ቀን ቀድመው በሕይወት ለተለዩ መነኵሲት የመቃብር ጉድጓድ ሲቆፍሩ የነበሩ ስድስት እድርተኞች እና አንድ የአብነት ተማሪ መኾናቸውን፣ ነዋሪዎቹ...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ግጭት ያለሕግ የታሰሩ ሰዎች ከ96 በላይ መድረሱ ተገለጸበአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ፣ ከዜይሴ ብሔረሰብ ቀበሌዎች የልዩ ወረዳ አደረጃጀት ጥያቄ ጋራ በተያያዘ ግጭት የታሰሩ ሰዎች ቁጥር ከ96 በላይ መድረሱን የገለጹ ቤተሰቦቻቸው፣ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውንና የተጠረጠሩበትንም ወንጀል እንዳላወቁ አስታውቀዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ የአካባቢውን ባለሥልጣናት ምላሽ እና አስተያየት ለማካተት ያደረግነው ጥረት፣ ስልካቸውን ስለማያነሡ አልተሳካም፡፡0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበትግራይ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች እየታየ ባለው የእንስሳት በሽታ አራት ሰዎች ሞቱበትግራይ ክልል፣ አንትራክስ ወይም በልማድ አባ ሰንጋ በተባለው የእንስሳት በሽታ፣ አራት ሰዎች መሞታቸውን፣ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በበሽታው የተያዘን የበሬ ሥጋ የተመገቡ ሌሎች ሰዎችም መታመማቸው ታውቋል። በክልሉ በጦርነቱ ወቅት ተቋርጦ ከቆየው የእንስሳት ክትባት ጋራ በተያያዘ፣ በሽታው በተለያዩ የክልሉ ወረዳዎች መስፋፋቱ ተገልጿል፡፡ በአሁኑ ወቅት የበሽታው ክትባት ወደ ክልሉ እየገባ እንደሚገኝ የተጠቆመ ሲኾን፣ ሣር በል የቤት እንስሳትን በወቅቱ...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMየአፍሪካ መከላከያ ባለሥልጣናት በቦትስዋና ሊመክሩ ነውሠላሳ የአፍሪካ ሃገራትን የሚወክሉ የመከላከያ ሃላፊዎች አህጉሪቱ በገጠማት የፀጥታ እና የመረጋጋት ተግዳሮቶች ላይ ለመነጋገር በመጪው ሳምንት ቦትስዋና ላይ የሁለት ቀናት ጉባኤ ይቀመጣሉ። ጉባኤው የተዘጋጀው ‘አፍሪኮም’ በመባል የሚታወቀው የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ዕዝ ሲሆን፣ ተመሳሳይ ጉባኤ መካሄድ ከጀመረበት ከእ.አ.አ 2017 ወዲህ በአህጉሪቱ ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ኮንዲሲ ዱቤ ከጋቦሮኔ የላከውን ዘገባ እንግዱ ወልዴ ወደ አማርኛ መልሶታል።0 Comments 0 Shares