የአሜሪካ ኀይሎች ቀይ ባሕር ላይ ስድስት የሁቲ ድሮኖችን ደመሰሱ
የዩናይትድ ስቴትስ ጦር፣ በቀይ ባሕር ላይ በኢራን በሚደገፉ የሁቲ ዐማፅያን የሚንቀሳቀሱ ስድስት ሰው አልባ አውሮፕላኖችን አወደመ።
ጥቃቱ የደረሰው፣ የሁቲ ዐማፅያን ሁለተኛው የንግድ መርከባቸው መስጠሙ በተረጋገጠበት ተመሳሳይ ቀን ነው፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ማዕከላዊ ዕዝ፣ ትላንት ኀሙስ በባሕሩ ላይ የነበሩ አራት ሰው አልባ መርከቦችንና ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ሁለት ድሮኖችን ማውደሙን አስታውቋል።
በጥቃቱ፣ በዩናይትድ ስቴትስ በኩል የተገለጸ...