በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት ስራ ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶች ተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት ሊሰጡ ነው

0
0

በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶችን ለተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት መስጫነት እያዘጋጃቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ከትራንስፖርት ባለስልጣንና ከአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ጋር በመሆን በእርጅና ምክንያት አገልግሎት ያቋረጡ አውቶቡሶችን መልሶ መጠቀም የሚያስችል ጥናት አካሂዷል።

አውቶቡሶቹ ለኢንተርኔት ካፌ፣ ለፀጉር ቤት፣ ለካፌና ሬስቶራንት፣ ለሸቀጣ ሸቀጥና ለቅርጻ ቅርጽ መሸጫነት በሚያመች መልኩ እየተጠገኑ መሆኑንና እየተጎተቱ ወደተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንደሚሰጡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ዘርዑ ስሙር ተናግረዋል።

ስራው የቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግር ከመፍጠር ባሻገር በመዲናዋ ያለውን የመስሪያ ቦታ ችግር በማቃለልና የስራ እድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት።

አውቶቡሶቹ ከኢንተርኔት አገልግሎት ባሻገር የጽህፈት መሳሪያ መሸጫ፣ የፕሪንትና ኮፒ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው የተጠገኑ በመሆኑ በርካታ ወጣቶች ተደራጅተው የመስራት እድል ያገኛሉ ብለዋል።

በመዲናዋ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ከ700 በላይ አንበሳ አውቶቡሶች መኖራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።

 

Like
1
ፍለጋ
Categories
Read More
Uncategorized
ወርቃማው ደብዳቤ !
(አሌክስ አብርሃም) እንዴት ናት ኢትዮጲያ እንዴት ነው አፈሩ ጤናቸው እንዴት ነው ጠቅላይ ሚንስትሩ ?ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህናናቸው...
By binid 2017-11-24 20:05:00 0 0
Uncategorized
ሰርጋቸው ደማቅ ስለነበር ለምን ይፋታሉ?
(አሌክስ አብርሃም) እንዴት ናችሁ ጓዶች ….ከሰሞኑ የፍች ወሬ በርከት ብሎ ሰነበተ ፌስቡክ ላይ? … ይች ፌስቡክ መቸም ፍች...
By binid 2017-11-25 13:29:51 0 0
Uncategorized
Selling
Product
By Hana 2017-11-25 17:05:20 5 0
Uncategorized
.me
About .ME Are you trying to find a way to take control of your online identity? Maybe trying to...
By Dawitda 2017-11-15 16:52:32 0 0
Uncategorized
በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት ስራ ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶች ተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት ሊሰጡ ነው
በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶችን ለተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት መስጫነት እያዘጋጃቸው መሆኑን የአዲስ አበባ...
By Dawitda 2017-12-22 09:06:30 0 0