ሰርጋቸው ደማቅ ስለነበር ለምን ይፋታሉ?

0
0

(አሌክስ አብርሃም)

እንዴት ናችሁ ጓዶች ….ከሰሞኑ የፍች ወሬ በርከት ብሎ ሰነበተ ፌስቡክ ላይ? … ይች ፌስቡክ መቸም ፍች ስትወድ በስመአብ !! እውነቴንኮ ነው ….እንትናና እንትና ተጋቡ የሚል ፖስት ያውም ሙሽራው ሱፍ ለብሶ ወገቡን ይዞ አንዴ እንደበረኛ ተወርውሮ ተኝቶ …አንዴ ፈረስ ላይ ነብስና ስጋው እየተሟገተ ፊቱ ‹‹አቫተር ›› መስሎ …. የተነሳውን ፎቶ ሁሉ ለጥፎ ሶስት ላይክና አራት ኮሜንት ብቻ ታያላችሁ ….‹‹ ተፋቱ ›› ሲባል ስምንት መቶ ላይክ አራት ሽ ኮሜንት ሶስት ሽ ሸር ! ውይ ፌስቡክ ፍች ስትወድ ይች ሾይጣን ሂሂ!አይዞን የሰው ባህሪ ነው !


የሰርግ ፎቶ ስል ምን ትዝ አለኝ …አንዴ ጓደኛችን አግብቶ ሰርግ ሄድንና የመስክ ፎቶ ተብሎ በቃ አገልግል ነሽ ሞሰብ ነሽ …ፈረስ ነሽ ጦርና ጋሻ …የቀረ ነገር የለም …አድዋ ዘማች መስለን ከአዲስ አበባ ወጣ ወዳለ ሜዳና ወንዝ ወዳለበት ቦታ ጎረፍን ! ፎቶ አንሽው እዛ ሜዳ ላይ ሙሽራውን ፍዳውን አሳየው ….‹‹እ …አሁን አንተ ከላይ እሷ ከታች …አሁን ደግሞ አንች ከላይ ሁነሽ ከንፈሩን በስሱ ትስሚዋለሽ …ሙሽራው ፈገግ አለ

(ምን አስገለፈጠው መቸም ህዝብ ፊት እንትን …አይደረግ ጅል…) እንላለን ፀሃዩ አማሮን …ሙሽራዋ ደግሞ ፍዝዝ ያለች ነገር ከንፈሩን እየተባለች ግንባሩ ላይ ቀይ ሊፒስቲኳን ለደፈችበት …(ወደፊት ሲጋቡ በመጥበሻ ግንባሩን እንደምትፈነክተው አመላካች ነው ሲል ከመካከላችን የነበረ አንድ የስነልቦና ባለሙያ ማብራሪያ ሰጠን…በነገራችን ላይ ይሄ የስነልቦና ባለሙያ በትንሽ ትልቁ ነገር እያለቀሰ እና ራሴን አጠፋለሁ እያለ ስንት ጊዜ መሰላችሁ በምክር ያተረፍነው ‹ተው እንጅ ምንድነው ተምሮ እንዳልተማረ መሆን› ብለን ) እና ‹‹የማታዋጣ ሚስት ግንባር ትስማለች›› የሚለው ተረት ‹‹የማያዋጣ ባል ቅንድብ ይስማል ›› የሚለውን አባባል ተክቶ ስራ ላይ የዋለው የዛን ቀን ነው !!

ከዛ….ሙሽራው እንደዛ ጅስሙ ግሎ በቃ ቶሎ መሽቶ ወደቤት ሂደን …ምናምን እያለ ሲደሳሰት ….የተረገመ ፎቶ አንሽ ምን ቢለው ጥሩ ነው ….አሁን ደግሞ ጫማህን አውልቅና እግርህን ወንዙ ውስጥ ዘፍዝፈው …እሰይ ! እንዲህ ቀዝቀዝ ይበል እንጅ ሃሃሃ ! ባል ከዛ ቀን ጀምሮ ቀዝቀዝ ያለ አባወራ ሆነ በቃ ! በተለይ ያሳዘነኝ …ፎቶ አንሽው ‹‹ አሁን ሙሽሪትን አንሳና ተሸከማት ›› ሲለው ዞር ብሎ እኛን አየን ….(ቅድም እሷ ከላይ አንተ ከታች ሲባል ያላስታወሰንን አሁን ያፈጣል እንዴ) አንዳንዱ ሰው ደስታውን እንደዶሮ አጥንት ብቻውን ቅርጥፍ ያደርግና ሸክሙ ላይ ‹‹ወዳጅ ለመቸ ነው ዘመድ ለክፉ ቀን…እርዱኝ እንጅ በኔ የደረሰው እህህ ምናምን ›› ይላችኋል …እዛው ተሸከም ባክህ ! በዚህ ፀሃይ እንኳን ያንተ ሚስት የያዝናት ሃይላንድ ውሃም ከብዳናለች !

ግን አልጨከንበትም እንደሬሳ እግርና ራሷን ይዘን እንደግሬደር ማፈሻ የተዘረጋ እጁ ላይ አሳቀፍነው (ደግሞ ፀጉሬን እንዳታበላሹ ነግሪያለሁ …ብላ ትቆጣለች እንዴ ኩርንችት ልንላት ነበር ሙሽራ ክቡር ነው ብለን ዝም አልን) በስንት መከራ እየተንገዳገደ አቅፏት ተነሳ …ፊቱ በቃ የኦሎምፒክ ክብደት አንሽ ነበር የሚመስለው! አንዳንድ ሚስቶች ደግሞ ሲታቀፉ ዝልፍልፍ የሚሉት ነገር አለ (አማላይ መኮኑ ነው) …ከምር! ማቀፉ ይቅር ሰው እንዴት መታቀፍ ያቅተዋል ….‹‹በመሃበር ታቀፊ አለ ክበበው) እንዲህ አይነት ፎቶ ስታዩ የሰርግ ፎቶ ሳይሆን ሙሽሪት ራሷን ስታ አፋፍሶ ይዟት ወደሆስፒታል የሚሮጥ ነው የሚመስለው ….

ወደዋናው ጉዳይ እንመለስ ኧረ ….(ምንድነው ስራ የላችሁም እንዴ ዝም ብላችሁ ትሰማላችሁ ….ወቸ ጉድ !)እና መቸስ በፍቅር ክንፍ እንደማለት ሁሉ አይንህን ላፈር መባባልም የነበረ ያለና የሚኖር ነው . . . ከሰሞኑ እህት እፀ ህይዎት ተፋታች መባሉን ተከትሎ ከሰፊው ህዝብ እስከታዋቂ ሰዎቻችን ወሬውን እንደጉድ እያራገቡት ነበር …የገረመኝ ነገር ታዲያ ‹‹እንደዚያ በደመቀ ሰርግ ተጋብተው እንዴት ይፋታሉ›› ብሎ እንደትልቅ ነጥብ ኮስተር ብሎ የሚከራከረው ሰው መብዛት ነው ! ጓዴ የሰርግ ድምቀት በለው … የመልክ ድምቀት በለው ሃብት በለው ….. ዘመድ በለው …. በሁለት ወንድና ሴት መሃል አንዴ አለመፈለግ ከነፈሰ ምንም ምድራዊ ሃይል እንደገና መፈለግን አያመጣውም !! እደግመዋለሁ ካልፈለክ ታንክ ቢደገንብህም አትፈልግም!

እና ሰው ደግሞ ካልፈለገ ሌላ ምንም ምክንያት አያስፈልገውም !በቃ አብሮ መሆን አልፈለገም !! ፍችን አልደግፍም ግን ሰው በቃኝ ብሎ ከሄደ በቃ በቃኝ ነው !! አንዳንዱ በሰው ህይዎት ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት ሁሉ ያምረዋል …የሆነ መፎክር ነገር

‹‹ አልፈልግሽም ማለት ህዝብን መናቅ ነው ›› 
‹‹ነው! ›› 
‹‹አገራችን በተያያዘችው የእድገትና ልማት ጎዳና የእገሊት ባሏን መፍታት ልማት ያደናቅፋል›› …
‹‹ያደናቅፋል!›› 
‹‹ለሰርጋቸው ያወጡት ብር ለመንገድ ስራ ቢውል ጥሩ ነበር ››
‹‹ነበር›› 
‹‹እሷ ማን ስለሆነች ነው የምትፋታው ››
‹‹ታው›› . . . ሃሃ

ወደዚህኛውም ጉዳይ ስንመጣ ውስጣቸውን እግዜር ይወቅ … ቢያንስ ለልጆቻቸው ሲሉ መታረቅ እና ሰከን ብለው ማሰብ ከቻሉ አሪፍ ! ካልሆነ ግን እሷም ቆንጆ ነች አሪፍ ተዋናይትም ነች…እሱም ፀዳ ያለ ሰው ነው….ሁለቱም ደግሞ ከወጣትነት ብዙም አራቁም ….እንግዲህ ከውጭ ማየት የሚቻለው ይሄን ብቻ ነው …እና …መልካም ህይዎት በየፊናቸው ! እትት ብትት የለም !

Search
Categories
Read More
Uncategorized
~~~~~~ Alert! Alert! Alert! ጥንቃቄ!!! ~~~~~
በሳዑዲ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን~~~~~~~~//~~~~~~~~//~~~~~~~~~ከነገ ማለትም እ.ኤ.አ ከኖቬምበር 15 ማለዳ ጀምሮ ላልተወሰኑ...
By Dawitda 2017-11-15 06:51:19 0 0
Uncategorized
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የተከታታይ ትምህርት መርሃ-ግብሮች ትኩረት ሊደረግባቸው ይገባል ተባለ፡፡
ተከታታይ የትምህርት መርሃ-ግብር አያሌ ዜጐችን በማታ፣ በክረምትና በእረፍት ቀናት ተምረው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ማስቻሉ በጥናት...
By Seller 2017-11-15 07:31:38 0 0
Uncategorized
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመሠራረት ምን ይመሥላል?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መሥሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ የሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አየር መንገድ ድርጅት ነው። አየር መንገዱ ከቀድሞው ትራንስ...
By Dawitda 2017-12-04 06:54:03 0 0
Uncategorized
ዘውዲቱ ሆስፒታል 5 የኩላሊት እጥበት መስጫ መሳሪያዎችን በወቅቱ አለመግዛቱ ችግር ፈጥሮብናል
ዘውዲቱ ሆስፒታል 5 የኩላሊት እጥበት መስጫ መሳሪያዎችን በወቅቱ አለመግዛቱ ችግር ፈጥሮብናል-ታካሚዎች ዘውዲቱ ሆስፒታል ከአንድ ዓመት በፊት ለአምስት...
By binid 2017-11-26 06:52:11 0 0
Uncategorized
አራዳ ይስፋፋ
አራዳ ይስፋፋ..!!!ሰገጤ ይነፋ..!!! በሚለው የዘውትር መግቢያ መፈክራችን ከዋናው ስቱዲዮ ሁነን የዛሬው የቅዳሜ ጭውቴአችንን በይፋ ጀምረናል...
By binid 2017-11-26 06:39:12 0 0