በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት ስራ ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶች ተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት ሊሰጡ ነው
በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶችን ለተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት መስጫነት እያዘጋጃቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው ከትራንስፖርት ባለስልጣንና ከአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ጋር በመሆን በእርጅና ምክንያት አገልግሎት ያቋረጡ አውቶቡሶችን መልሶ መጠቀም የሚያስችል ጥናት አካሂዷል።
አውቶቡሶቹ ለኢንተርኔት ካፌ፣ ለፀጉር ቤት፣ ለካፌና ሬስቶራንት፣ ለሸቀጣ ሸቀጥና ለቅርጻ ቅርጽ መሸጫነት በሚያመች መልኩ እየተጠገኑ መሆኑንና እየተጎተቱ ወደተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንደሚሰጡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ዘርዑ ስሙር ተናግረዋል።
ስራው የቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግር ከመፍጠር ባሻገር በመዲናዋ ያለውን የመስሪያ ቦታ ችግር በማቃለልና የስራ እድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት።
አውቶቡሶቹ ከኢንተርኔት አገልግሎት ባሻገር የጽህፈት መሳሪያ መሸጫ፣ የፕሪንትና ኮፒ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው የተጠገኑ በመሆኑ በርካታ ወጣቶች ተደራጅተው የመስራት እድል ያገኛሉ ብለዋል።
በመዲናዋ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ከ700 በላይ አንበሳ አውቶቡሶች መኖራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።
Search
Categories
- Home
- Wellness
- Theater
- Sports
- Shopping
- Religion
- Party
- Other
- Networking
- Music
- Literature
- Art
- Health
- Gardening
- Games
- Food
- Fitness
- Film
- Drinks
- Dance
- Crafts
- Causes
Read More
From Crisis to Comeback: How ORM Agencies Handle Online Attacks
In today’s digital-first world, a brand’s reputation can make or break its success....
Champion marathon runner Zenash Gezmu who fled Ethiopia found beaten to death by another refugee in Paris
A champion marathon runner who fled Ethiopia six years ago for a better life in Europe has been...
የመጀምሪያዋ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጦር መርከብ ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም ከመያዟ በፊት P.C. 1616 ትባል ነበር። ይህች ዘመናዊ መርከብ ከአሜሪካን መንግስት በእርዳታ የተገኘች ነበረች።
1616 ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም እንዲወጣላት በማስፈለጉ በጊዜው የነበረውን ተጨባጭ ሁ...