በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት ስራ ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶች ተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት ሊሰጡ ነው
Posted 2017-12-22 09:06:30
0
0
በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶችን ለተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት መስጫነት እያዘጋጃቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው ከትራንስፖርት ባለስልጣንና ከአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ጋር በመሆን በእርጅና ምክንያት አገልግሎት ያቋረጡ አውቶቡሶችን መልሶ መጠቀም የሚያስችል ጥናት አካሂዷል።
አውቶቡሶቹ ለኢንተርኔት ካፌ፣ ለፀጉር ቤት፣ ለካፌና ሬስቶራንት፣ ለሸቀጣ ሸቀጥና ለቅርጻ ቅርጽ መሸጫነት በሚያመች መልኩ እየተጠገኑ መሆኑንና እየተጎተቱ ወደተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንደሚሰጡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ዘርዑ ስሙር ተናግረዋል።
ስራው የቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግር ከመፍጠር ባሻገር በመዲናዋ ያለውን የመስሪያ ቦታ ችግር በማቃለልና የስራ እድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት።
አውቶቡሶቹ ከኢንተርኔት አገልግሎት ባሻገር የጽህፈት መሳሪያ መሸጫ፣ የፕሪንትና ኮፒ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው የተጠገኑ በመሆኑ በርካታ ወጣቶች ተደራጅተው የመስራት እድል ያገኛሉ ብለዋል።
በመዲናዋ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ከ700 በላይ አንበሳ አውቶቡሶች መኖራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።
ፍለጋ
Categories
- Home
- Wellness
- Theater
- Sports
- Shopping
- Religion
- Party
- Other
- Networking
- Music
- Literature
- Art
- Health
- Gardening
- Games
- Food
- Fitness
- Film
- Drinks
- Dance
- Crafts
- Causes
Read More
NFL Network predicts result of every Bears game in 2023
The Chicago Bears are coming off a three-win season where they made the No. 1 choice in the NFL...
Why Choosing the Right Microsoft 365 Services Provider Matters for Healthcare Organizations
Healthcare organizations are experiencing unprecedented digital transformation as they strive to...
የዚምባብዌ ጦር ገዢው ፓርቲ ላይ በሚደረገው ጣልቃ ገብነት ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጠ
ብዙም ያልተለመደው የጣልቃ ገብነት ጉዳይ የተከሰተው ሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ምክትላቸው ኤመርሰን ምናንጋግዋን ከስራ ካሰናበቱ በኋላ ነው። ከ90...
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)(ማስጠንቀቂያ….ይህ ጽሁፍ ልክ እንደ እሁድ ረዥም ስለሆነ ስራ ያለበት ሰው ከእሁድ ውጪ...