በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት ስራ ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶች ተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት ሊሰጡ ነው

በመዲናዋ በእርጅና ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ አንበሳ አውቶቡሶችን ለተንቀሳቃሽ የንግድ አገልግሎት መስጫነት እያዘጋጃቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው ከትራንስፖርት ባለስልጣንና ከአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ጋር በመሆን በእርጅና ምክንያት አገልግሎት ያቋረጡ አውቶቡሶችን መልሶ መጠቀም የሚያስችል ጥናት አካሂዷል።
አውቶቡሶቹ ለኢንተርኔት ካፌ፣ ለፀጉር ቤት፣ ለካፌና ሬስቶራንት፣ ለሸቀጣ ሸቀጥና ለቅርጻ ቅርጽ መሸጫነት በሚያመች መልኩ እየተጠገኑ መሆኑንና እየተጎተቱ ወደተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንደሚሰጡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ዘርዑ ስሙር ተናግረዋል።
ስራው የቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግር ከመፍጠር ባሻገር በመዲናዋ ያለውን የመስሪያ ቦታ ችግር በማቃለልና የስራ እድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት።
አውቶቡሶቹ ከኢንተርኔት አገልግሎት ባሻገር የጽህፈት መሳሪያ መሸጫ፣ የፕሪንትና ኮፒ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው የተጠገኑ በመሆኑ በርካታ ወጣቶች ተደራጅተው የመስራት እድል ያገኛሉ ብለዋል።
በመዲናዋ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ከ700 በላይ አንበሳ አውቶቡሶች መኖራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።

Search
Categories
- Home
- Wellness
- Theater
- Sports
- Shopping
- Religion
- Party
- Other
- Networking
- Music
- Literature
- Art
- Health
- Gardening
- Games
- Food
- Fitness
- Film
- Drinks
- Dance
- Crafts
- Causes
Read More
ወርቃማው ደብዳቤ !
(አሌክስ አብርሃም)
እንዴት ናት ኢትዮጲያ እንዴት ነው አፈሩ ጤናቸው እንዴት ነው ጠቅላይ ሚንስትሩ ?ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህናናቸው...
Call girls in dubai +971565904081 Under 500 Aed Call Girls
Call girls in dubai +971565904081 Under 500 Aed Call Girls
She left. She said that Dad told her...
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)(ማስጠንቀቂያ….ይህ ጽሁፍ ልክ እንደ እሁድ ረዥም ስለሆነ ስራ ያለበት ሰው ከእሁድ ውጪ...
በህይወት እስካለህ ልትሳሳት ፣ ልትወድቅ ትቸላለህ
በህይወት እስካለህ ልትሳሳት ፣ ልትወድቅ ትቸላለህ ፣ ሰዎች ላይቀበሉህ ይችላሉ ፣ ወይም ሀሳብህን ላይረዱህ ፣ ቦታ ላይሰጡህ ይችላሉ ፣ በእጅህ ላይ ያለው...