የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ ወሰደ

የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
በዚህ መሰረት የድርጅቱ ሊቀ መንበር አቶ አባይ ወልዱ ከድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው ተነስተው በድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲያገለግሉ ወስኗል።
በተጨማሪም የድርጅቱ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ በየነ ምክሩም ወደ ድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲሰሩ መወሰኑን ድርጅቱ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ከዚህ ባለፈም የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወይዘሮ አዜብ መስፍንን ከስራ አስፈጻሚ አባልነታቸው እና ማዕከላዊ ኮሚቴው ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑንም ገልጿል።
ድርጅቱ ከዚህ በተጨማሪም ለሌሎች ሁለት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
እርምጃው ማዕከላዊ ኮሚቴው ያካሄደውን ጥልቅ ግምገማ ተከትሎ የተወሰደ ነው።
ማዕከላዊ ኮሚቴው ባለፈው ሳምነት ባወጣው መግለጫ በአመራር ስትራቴጂካዊ ፖለቲካዊ ሁነቶች፣ ሁለንተናዊ የልማታዊ ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥ እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ በጥልቅ በመገምገም ያሉትን መሰረታዊ ክፍተቶች በዝርዝር ማየቱን ገልፆ ነበር።
በትግልና በመርህ የተመሰረተ አንድነት አለመኖር፣ በመጠቃቃትና መከላከል ዝምድና ላይ መመስረት፣ የፀረ ዴሞክራሲ ጥልቅ አስተሳሰብና ተግባራት መኖራቸውን መገምገሙንም በመግለጫው ማስታወቁ ይታወሳል።
በተጨማሪም የወጣቱን ትውልድ እና የምሁሩን አቅም በመገንባት፣ በማሰለፍና ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ መሰረታዊ ጉድለቶች መኖራቸውን ገምግሞ ነበር።
በክልሉም ትራንስፎርሜሽን ከማረጋገጥ አኳያ መሰረታዊ ስትራቴጂካዊ የአመራር ችግር እንደነበረበት በመገምገም፥ ባለፉት አመታት በተደረገው እንቅስቃሴ በገጠርና ከተማ የተመዘገቡ የልማት ድሎች መኖራቸውን ያረጋገጠ ቢሆንም ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳካት አኳያ የህዝቡ ተጠቃሚነት ከፍላጎቱ ጋር ሲመዘን ግን መሰረታዊ ችግሮች እንደነበሩበት በመገምግም ማረጋገጡንም ነበር በመግለጫው የጠቀሰው።
ማእከላዊ ኮሚቴው በቀሪ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ላይ ጥልቅ ሂስና ግለ ሂስ የቀጠለ ሲሆን፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የአመራር መልሶ ማደራጀት እንደሚያደርግ አስታውቋል ።
በሙሉጌታ አፅብሃ
በዚህ መሰረት የድርጅቱ ሊቀ መንበር አቶ አባይ ወልዱ ከድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው ተነስተው በድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲያገለግሉ ወስኗል።
በተጨማሪም የድርጅቱ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ በየነ ምክሩም ወደ ድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲሰሩ መወሰኑን ድርጅቱ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ከዚህ ባለፈም የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወይዘሮ አዜብ መስፍንን ከስራ አስፈጻሚ አባልነታቸው እና ማዕከላዊ ኮሚቴው ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑንም ገልጿል።
ድርጅቱ ከዚህ በተጨማሪም ለሌሎች ሁለት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
እርምጃው ማዕከላዊ ኮሚቴው ያካሄደውን ጥልቅ ግምገማ ተከትሎ የተወሰደ ነው።
ማዕከላዊ ኮሚቴው ባለፈው ሳምነት ባወጣው መግለጫ በአመራር ስትራቴጂካዊ ፖለቲካዊ ሁነቶች፣ ሁለንተናዊ የልማታዊ ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥ እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ በጥልቅ በመገምገም ያሉትን መሰረታዊ ክፍተቶች በዝርዝር ማየቱን ገልፆ ነበር።
በትግልና በመርህ የተመሰረተ አንድነት አለመኖር፣ በመጠቃቃትና መከላከል ዝምድና ላይ መመስረት፣ የፀረ ዴሞክራሲ ጥልቅ አስተሳሰብና ተግባራት መኖራቸውን መገምገሙንም በመግለጫው ማስታወቁ ይታወሳል።
በተጨማሪም የወጣቱን ትውልድ እና የምሁሩን አቅም በመገንባት፣ በማሰለፍና ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ መሰረታዊ ጉድለቶች መኖራቸውን ገምግሞ ነበር።
በክልሉም ትራንስፎርሜሽን ከማረጋገጥ አኳያ መሰረታዊ ስትራቴጂካዊ የአመራር ችግር እንደነበረበት በመገምገም፥ ባለፉት አመታት በተደረገው እንቅስቃሴ በገጠርና ከተማ የተመዘገቡ የልማት ድሎች መኖራቸውን ያረጋገጠ ቢሆንም ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳካት አኳያ የህዝቡ ተጠቃሚነት ከፍላጎቱ ጋር ሲመዘን ግን መሰረታዊ ችግሮች እንደነበሩበት በመገምግም ማረጋገጡንም ነበር በመግለጫው የጠቀሰው።
ማእከላዊ ኮሚቴው በቀሪ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ላይ ጥልቅ ሂስና ግለ ሂስ የቀጠለ ሲሆን፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የአመራር መልሶ ማደራጀት እንደሚያደርግ አስታውቋል ።
በሙሉጌታ አፅብሃ
Search
Categories
- Home
- Wellness
- Theater
- Sports
- Shopping
- Religion
- Party
- Other
- Networking
- Music
- Literature
- Art
- Health
- Gardening
- Games
- Food
- Fitness
- Film
- Drinks
- Dance
- Crafts
- Causes
Read More
አንዳንድ ቅዳሜዎች
አንዳንድ ቅዳሜዎች፡በጣም ጠፋሁ አይደል!!; አይ ኖው…. አይ ኖው….አይ ሚስ ዩ ቱ ጋይስ፡፡ያው መጥፋቴ የቢዴና ነገር ሆኖብኝ...
CHÍNH HÃNG" Xe Nâng Điện NISSAN 1.5 Tấn YU01F15 (FBR15) Đủ hồ sơ hải quan kiểm định
Bạn đang tìm kiếm một giải pháp nâng hạ hàng hóa tối ưu cho kho...
የዚምባብዌ ጦር ገዢው ፓርቲ ላይ በሚደረገው ጣልቃ ገብነት ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጠ
ብዙም ያልተለመደው የጣልቃ ገብነት ጉዳይ የተከሰተው ሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ምክትላቸው ኤመርሰን ምናንጋግዋን ከስራ ካሰናበቱ በኋላ ነው። ከ90...
እንቆቅልሽ የሆነው የወተት ምርት
ኢትዮጵያ በቀንድ ከብቶች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚውን ሥፍራ፣ በዓለም ከ10 አገሮች መካከል አንዷ ብትሆንም ከወተት ሀብቷ ማግኘት የሚገባትን ያህል ጥቅም...