ሁለቱ ወንድማማቾች ___

0
0

 በአንድ የገጠር መንደር በቤተሰቦቻቸው የእርሻ ማሳ በጋራ እያመረቱ የሚተዳደሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ አንደኛው ትዳር መስርቶ ብዙ ቤተሰብ የሚያስተዳደር ሲሆን አንደኛው ግን ገና አላገባም ብቻውን ነው የሚኖር፡፡ በምርት መሰብሰቢያ ወቅት ያገኙትን ምርት እኩል ይካፈሉ ነበር፡፡ ታዲያ አንድ ቀን ትዳር ያልመሰረተው ለእራሱ እንዲህ አለ፡፡ “ያገኘነውን ምርት እኩል መካፈል ፍተሃዊ አይደለም፡፡ እኔ ብቻየን ስለሆንኩ ትንሽ ነገር ነው ሊበቃኝ የሚችለው፡፡” እንዲህ ብሎ መሸት ሲልለት ጨለማውን ተግነ አድርጎ ከጎተራው ኬሻ ሙሉ ጥራጥሬ እያነሳ በቤታቸው መካከል ባለው መስክ አቋርጦ ከወንድሙ ጎተራ ይሞላለት ነበር፡፡ በተመሳመሳይ ሁኔታ ትዳር የመሰረተው ወንድሙም ለእራሱ እንዲህ ይላል “ምርታችንን እኩል መካፈላችን ትክክል አይደለም፡፡ ሁኖ ሁኖ እኔ ባለ ትዳር ነኝ በመጭዎቹ አመታት አንዳች ነገር ቢፈጠር እንኳን ልጆቼና ሚስቴ ይንከባከቡኛል፡፡ ይሄ ወንድሜ ግን ብቻውን ነው፡፡ ማንም የሚንከባከበው የለውም ስለሆነም” አለና መሸት ሲልለት ጨለማውን ተግነ አድርጎ ኬሻ ሙሉ ጥራ ጥሬ እየወሰደ ከላጤ ወንድሙ ጎተራ ይጨምራል፡፡ እንዲህ እንዲህ እያሉ ዓመቱ ተጋመሰ የእህል ጎተራቸው ያልቀነሰበት ምክንያት ግን እንቆቅልሽ ሆኖባቸዋል፡፡ ከዛም አንድ ቀን ምሽት ሁለቱም እንደልማዳቸው አንደኛው ላንደኛው ኬሻ ሙሉ ጥራጥሬውን ይዘው ሲተላለፉ ሁኔታዎች ተገጣጠሙና መንገድ ላይ ተጋጩ፡፡ ቀስ አድርገው ሸክማቻን አውርደው ሲተያዩ ወደንድማማቾቹ ነበሩ፡፡ በልባዊ ፍቅር ተቃቀፉ፡፡ ፊት ለፊት ተነጋግረው የበለጠውን አንደኛው መውሰድ እንዲችል ማድረግ ጠፍቷቸው አይደለም ግን አንተ ትብስ አንተ ትብስ እየተባባሉ ውሳኔ ላይ መድረስ እንደማይችሉ ስላወቁ የፈጠሩት መላ ይመስላል፡፡ እንኳንስ ስጡ ሳይባሉ ለመስጠት መፍቀድ ቀርቶ ቢጠየቁ እንኳ እኩል ድርሻየ ነው ማለት በሚቻልበት ሁኔታ የበለጠውን ለመስጠት መሻት ከልባዊ ፍቀር ውጭ ሊመጣ አይችልም፡፡ ለሰጨውም ሆነ ለተቀባዩ ሳይቀንስ የሚሰጥ ስጦታ ልባዊ ፍቅር ብቻ ነው፡፡ እንዲህ አይነታ ፍቀር ይስጠን ነው የሚባለው፡፡ ምንጭ፡ Story of Two Brothers (#ምስጋናው ግሸን ወልደ አገሬ) 17-09-2007 ዓ.ም

Like
1
ፍለጋ
Categories
Read More
Uncategorized
70 ሜትር ከፍታ ባለው ገመድ ላይ የተራመደው ግለሰብ አዲስ ክብረ ወሰን ይዟል
ከመሬት230 ጫማ ወይም 70 ሜትር ከፍታ ላይ በታሰረ ቀጭን ገመድ ላይ የተራመደው ግለሰብ አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ይዟል። ናታን ፓውሊን የተባለው...
By Dagmawisol 2017-12-15 06:18:58 0 0
Uncategorized
ልክ የዛሬ 21 ዓመት ይህ ሆኗል
በደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው የኮሞሮስ ደሴት ተመራጭ የጎብኚዎች መዳረሻ ስፍራ ነች። በህንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ሲዝናኑ የነበሩ ጎብኚዎች እና...
By Dagmawisol 2017-11-23 06:15:19 1 0
Sports
Giants chasing products and services in direction of situations they generated ?'Valentine's Opinions'podcast
The Refreshing York Giants experienced a chaotic working day upon Giants waived advantage...
By BgmntFtball BgmntFtball 2026-02-06 06:42:36 0 0
Uncategorized
የመጀምሪያዋ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጦር መርከብ ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም ከመያዟ በፊት P.C. 1616 ትባል ነበር። ይህች ዘመናዊ መርከብ ከአሜሪካን መንግስት በእርዳታ የተገኘች ነበረች።
1616 ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም እንዲወጣላት በማስፈለጉ በጊዜው የነበረውን ተጨባጭ ሁ...
By Dagmawisol 2017-12-16 09:06:27 0 0
Uncategorized
‹‹በህልም የተፈጠረ መወስለት ከሐጢያት ይቆጠር ይሆን?››
‹‹በህልም የተፈጠረ መወስለት ከሐጢያት ይቆጠር ይሆን?››(አሳዬ ደርቤ)እንዴት ዋላችሁ ምዕመናን? እኔ...
By Assaye Derbie 2017-11-12 13:09:47 0 0