• https://www.ahadujobs.com/job-detail/job-accountant-1783
    https://www.ahadujobs.com/job-detail/job-accountant-1783
    WWW.AHADUJOBS.COM
    Berchaco Ethiopia Plc
    BA Degree in Accounting or related 2 years of related experience of FMCG experience is advantageous
    0 Comments 0 Shares
  • ፍርድ ቤቱ ቅቤን ከባእድ ነገር ጋር ደባልቀው ሸጠዋል ያላቸውን ሁለት ግለሰቦች በእስራትና በገንዘብ ቀጣ – ጎባ ሚያዝያ 19/2009 የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቅቤን ከባእድ ነገር ጋር ደባልቀው ሸጠዋል ባላቸው ሁለት ተከሳሾች ላይ የአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ወሰነ፡፡

    ፍርድ ቤቱ አበበች መዘንጊያና ፀሃይ ተሾመ በተባሉ ተከሳሾች ላይ የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው ትናንት በዋለው ችሎት ነው።

    ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን የወሰነው ተከሳሾቹ ሰኔ 25 ቀን 2008 በባሌ ጎባ ከተማ 04 ቀበሌና በሌሎች አካባቢዎች በመዘዋወር ከባእድ ነገር ጋር የተቀላቀለ ቅቤ ለግለሰቦች መሸጣቸው በማስረጃ በመረጋገጡ መሆኑን የፍርድ ቤቱ ዳኛ ደረጃ መኮንን ገልጸዋል።

    ከባዕድ ነገር ጋር የተቀላቀለው ቅቤ በኤግዚብትነት ተይዞ ናሙናው ለኢተዮዽያ የጥራት ደረጃዎች መዳቢ ባለሥልጣን የተላከ ሲሆን ምንም አይነት የንጹህ ቅቤ በህሪ እንደሌለው በተካሄደው ምርመራ መረጋገጡን ተናግረዋል።

    ተከሳሾቹ ድርጊቱን አልፈጸምንም ብለው ቢከራከሩም የቀረበባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻላቸው ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቅጣት ውሳኔውን ሊያስተላለፍ ችሏል።

    ተከሳሾቹ ከዚህ በፊት ምንም ዓይነት የክስ ቻርጅ እንደሌለባቸውና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸው እንደ ፍርድ ማቀለያ ተይዞ እያንዳንዳቸው በአምስት ዓመት ፅኑ እስራትና በ2 ሺህ 500 ብር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኖባቸዋል – ENA
    ፍርድ ቤቱ ቅቤን ከባእድ ነገር ጋር ደባልቀው ሸጠዋል ያላቸውን ሁለት ግለሰቦች በእስራትና በገንዘብ ቀጣ – ጎባ ሚያዝያ 19/2009 የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቅቤን ከባእድ ነገር ጋር ደባልቀው ሸጠዋል ባላቸው ሁለት ተከሳሾች ላይ የአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት ወሰነ፡፡ ፍርድ ቤቱ አበበች መዘንጊያና ፀሃይ ተሾመ በተባሉ ተከሳሾች ላይ የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው ትናንት በዋለው ችሎት ነው። ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን የወሰነው ተከሳሾቹ ሰኔ 25 ቀን 2008 በባሌ ጎባ ከተማ 04 ቀበሌና በሌሎች አካባቢዎች በመዘዋወር ከባእድ ነገር ጋር የተቀላቀለ ቅቤ ለግለሰቦች መሸጣቸው በማስረጃ በመረጋገጡ መሆኑን የፍርድ ቤቱ ዳኛ ደረጃ መኮንን ገልጸዋል። ከባዕድ ነገር ጋር የተቀላቀለው ቅቤ በኤግዚብትነት ተይዞ ናሙናው ለኢተዮዽያ የጥራት ደረጃዎች መዳቢ ባለሥልጣን የተላከ ሲሆን ምንም አይነት የንጹህ ቅቤ በህሪ እንደሌለው በተካሄደው ምርመራ መረጋገጡን ተናግረዋል። ተከሳሾቹ ድርጊቱን አልፈጸምንም ብለው ቢከራከሩም የቀረበባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻላቸው ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቅጣት ውሳኔውን ሊያስተላለፍ ችሏል። ተከሳሾቹ ከዚህ በፊት ምንም ዓይነት የክስ ቻርጅ እንደሌለባቸውና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸው እንደ ፍርድ ማቀለያ ተይዞ እያንዳንዳቸው በአምስት ዓመት ፅኑ እስራትና በ2 ሺህ 500 ብር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኖባቸዋል – ENA
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ3 ቢሊየን ብር ወጪ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው።

    “ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራው የገበያ ማዕከል ግንባታው በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አክሲዮን ማህበር ይከናወናል ነው የተባለው።

    ይህ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል በ125 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ የሚያርፍ ሲሆን፥ ጠቅላላ የግቢው ስፋት 250 ሺህ ካሬ ሜትር ይሸፍናል።

    የህዳሴ ግራንድ ሞል ስራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ መኮንን በሰጡት መግለጫ፥ የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ከሚገኙት በስፋቱና በዘመናዊነቱ የላቀ ይሆናል።

    ግንባታው የከተማ አስተዳደሩ ለአክሲዮን ማህበሩ ካመቻቻቸው ዘጠኝ ቦታዎች በአንዱ ላይ ይከናወናል።

    የገበያ ማዕከሉ በውስጡ 5 ሺህ ሱቆች፣ 2 ዘመናዊ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች፣ ባንክና ኢንሹራንስ እንዲሁም ካፌና ሬስቶራንቶችን የሚይዝ ነው።

    ማዕከሉ በአንድ ጊዜ 8 ሺህ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ፥ እንዲሁም የመኖሪያ አፓርታማዎች እንደሚኖሩትም ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል።

    ግንባታው ሲጠናቀቅ ለ35 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል እንደሚፈጥር ለኢዜአ የገለጹት አቶ ደረጀ፥ ነጋዴውና ሸማቹ ግብይታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

    ግንባታውን ለማስጀመር ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ ለማወዳደር ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

    የገበያ ማዕከሉ ግንባታ በሶስት ዓመት ጊዜ ተጠናቆ ስራ እንደሚጀምርም አቶ ደረጀ ጠቁመዋል።
    አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ3 ቢሊየን ብር ወጪ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው። “ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራው የገበያ ማዕከል ግንባታው በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አክሲዮን ማህበር ይከናወናል ነው የተባለው። ይህ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል በ125 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ የሚያርፍ ሲሆን፥ ጠቅላላ የግቢው ስፋት 250 ሺህ ካሬ ሜትር ይሸፍናል። የህዳሴ ግራንድ ሞል ስራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ መኮንን በሰጡት መግለጫ፥ የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ከሚገኙት በስፋቱና በዘመናዊነቱ የላቀ ይሆናል። ግንባታው የከተማ አስተዳደሩ ለአክሲዮን ማህበሩ ካመቻቻቸው ዘጠኝ ቦታዎች በአንዱ ላይ ይከናወናል። የገበያ ማዕከሉ በውስጡ 5 ሺህ ሱቆች፣ 2 ዘመናዊ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች፣ ባንክና ኢንሹራንስ እንዲሁም ካፌና ሬስቶራንቶችን የሚይዝ ነው። ማዕከሉ በአንድ ጊዜ 8 ሺህ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ፥ እንዲሁም የመኖሪያ አፓርታማዎች እንደሚኖሩትም ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል። ግንባታው ሲጠናቀቅ ለ35 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል እንደሚፈጥር ለኢዜአ የገለጹት አቶ ደረጀ፥ ነጋዴውና ሸማቹ ግብይታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። ግንባታውን ለማስጀመር ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ ለማወዳደር ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። የገበያ ማዕከሉ ግንባታ በሶስት ዓመት ጊዜ ተጠናቆ ስራ እንደሚጀምርም አቶ ደረጀ ጠቁመዋል።
    WWW.FANABC.COM
    FBC - በአዲስ አበባ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በ3 ቢሊየን ብር ሊገነባ ነው
    አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ3 ቢሊየን ብር ወጪ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው። “ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራው የገበያ ማዕከል ግንባታው በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አ...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 20 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም መደበኛ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ሊያካሂድ ነው።

    ነገ እና ከነገ በስቲያ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከተ ጥናትና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች ላይ ሪፖርት ይቀርባል።

    በጉባኤው በአለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ ምክክር እንደሚካሄድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አመልክቷል።

    ከዚህ ባለፈም በአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የመፍትሄ ሃሳቦች ዙሪያም ምክክር ይካሄዳል ነው የተባለው።

    በጉባኤው ህግ አውጭዎች፣ የሲቪል ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃንና የተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

    ተሳታፊዎቹን ጨምሮ ለዘርፉ ባለድርሻ አካላት፣ ለቢዝነስ ሰዎችና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይሰጣልም ተብሏል።

    ጉባኤው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከተመድ የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም ጋር በመሆን በቅንጅት ያዘጋጁት ነው።

    የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም በርካታ አባል ሃገራት ያሉት ሲሆን፥ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ሳይንሳዊ ጥናት እያደረገ የጥናቱን ግኝት ይፋ ያደርጋል።
    አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 20 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም መደበኛ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ሊያካሂድ ነው። ነገ እና ከነገ በስቲያ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከተ ጥናትና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች ላይ ሪፖርት ይቀርባል። በጉባኤው በአለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ ምክክር እንደሚካሄድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አመልክቷል። ከዚህ ባለፈም በአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የመፍትሄ ሃሳቦች ዙሪያም ምክክር ይካሄዳል ነው የተባለው። በጉባኤው ህግ አውጭዎች፣ የሲቪል ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃንና የተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል። ተሳታፊዎቹን ጨምሮ ለዘርፉ ባለድርሻ አካላት፣ ለቢዝነስ ሰዎችና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይሰጣልም ተብሏል። ጉባኤው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከተመድ የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም ጋር በመሆን በቅንጅት ያዘጋጁት ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም በርካታ አባል ሃገራት ያሉት ሲሆን፥ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ሳይንሳዊ ጥናት እያደረገ የጥናቱን ግኝት ይፋ ያደርጋል።
    WWW.FANABC.COM
    FBC - የተመድ የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም ጉባኤ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
    አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 20 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ተቋም መደበኛ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ሊያካሂድ ነው። ነገ እና ከነገ በስቲያ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከ...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቻይና መንግስት የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት የሚያደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር 8 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ግምት ያለው የሰብአዊ ድጋፍ አድርጓል።

    ድጋፉ በተለይ ለአልሚ ምግብ እጥረት ለተጋለጡ 277 ሺህ ህጻናት እና ሴቶች አስቸኳይ እርዳታዎችን ለመስጠት ያገዛል ተብሏል።

    በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ላ ይፋን በእርዳታ ርክክቡ ወቅት እንዳሉት፥ ቻይና የኢትዮጵያ ወዳጅ ሀገር በመሆኗ የተቻላትን ድጋፍ እያደረገች ነው፡፡

    “በማደግ ላይ የምንገኝ ሀገር ብንሆንም በአለም ምግብ ድርጅት አማካኝነት ለሌሎች ሀገራት ድጋፍ ማደረግ አለብን” ብለዋል አምባሳደሩ፡፡

    የኢትዮጵያ መንግስት በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎች አስቸኳይ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎችን በተመለከተ እያደረገ ያለውን ጥረት ያደነቁት አምባሳደሩ፥ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን የተፈጥሮ አደጋ ለመቀነስ በቁርጠኝነት መስራት ይኖርበታል ብለዋል።

    በኢትዮጵያ የአለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ጆን አይሊፍ በበኩላቸው፥ ቻይና በአንዳንድ አካባቢዎች በድርቅ ሳቢያ ለተጎዱ ኢትዮጵውያን እያደረገች ያለችውን አስተዋጽኦ አድንቀው፥ በአሁኑ ወቅት በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው ድርቅ ከ50 አመታት ወዲህ የከፋ መሆኑን ጠቁመዋል።

    የኢትዮጵያ መንግስት በራሱ አቅም ደርቁን ለመቋቋም እና ለዜጎቹ በወቅቱ አስቸኳይ እርዳታ እየሰጠ መሆኑን ያደነቁት ዳይሬክተሩ፥ አለም አቀፉ ማህበረሰብም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

    በዚህ ወቅት ቻይና ያደረገችው እርዳታንም በምሳሌነት ጠቅሰዋል፡፡

    የኢትዮጵያ መንግስት የአልሚ ምግብ እጥረት ያለባቸው ህጻናት ቁጥርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ስራ እየሰራ መሆኑን የአለም ምግብ ፕሮገራም በደረ ገጹ የጠቀሰ ሲሆን፥ 40 በመቶ ከሚሆኑ ህጻናት ውስጥ 9 በመቶው የመቀጨር ችግር ያሉባቸው በመሆኑ ችግሩን ለመቀነስ ብርቱ ጥረት እንደሚጠይቅ ጠቁሟል፡፡

    ምንጭ ፦http://www.vanguardngr.com
    አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቻይና መንግስት የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት የሚያደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር 8 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ግምት ያለው የሰብአዊ ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉ በተለይ ለአልሚ ምግብ እጥረት ለተጋለጡ 277 ሺህ ህጻናት እና ሴቶች አስቸኳይ እርዳታዎችን ለመስጠት ያገዛል ተብሏል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ላ ይፋን በእርዳታ ርክክቡ ወቅት እንዳሉት፥ ቻይና የኢትዮጵያ ወዳጅ ሀገር በመሆኗ የተቻላትን ድጋፍ እያደረገች ነው፡፡ “በማደግ ላይ የምንገኝ ሀገር ብንሆንም በአለም ምግብ ድርጅት አማካኝነት ለሌሎች ሀገራት ድጋፍ ማደረግ አለብን” ብለዋል አምባሳደሩ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎች አስቸኳይ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎችን በተመለከተ እያደረገ ያለውን ጥረት ያደነቁት አምባሳደሩ፥ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን የተፈጥሮ አደጋ ለመቀነስ በቁርጠኝነት መስራት ይኖርበታል ብለዋል። በኢትዮጵያ የአለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ጆን አይሊፍ በበኩላቸው፥ ቻይና በአንዳንድ አካባቢዎች በድርቅ ሳቢያ ለተጎዱ ኢትዮጵውያን እያደረገች ያለችውን አስተዋጽኦ አድንቀው፥ በአሁኑ ወቅት በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው ድርቅ ከ50 አመታት ወዲህ የከፋ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በራሱ አቅም ደርቁን ለመቋቋም እና ለዜጎቹ በወቅቱ አስቸኳይ እርዳታ እየሰጠ መሆኑን ያደነቁት ዳይሬክተሩ፥ አለም አቀፉ ማህበረሰብም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። በዚህ ወቅት ቻይና ያደረገችው እርዳታንም በምሳሌነት ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት የአልሚ ምግብ እጥረት ያለባቸው ህጻናት ቁጥርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ስራ እየሰራ መሆኑን የአለም ምግብ ፕሮገራም በደረ ገጹ የጠቀሰ ሲሆን፥ 40 በመቶ ከሚሆኑ ህጻናት ውስጥ 9 በመቶው የመቀጨር ችግር ያሉባቸው በመሆኑ ችግሩን ለመቀነስ ብርቱ ጥረት እንደሚጠይቅ ጠቁሟል፡፡ ምንጭ ፦http://www.vanguardngr.com
    WWW.FANABC.COM
    FBC - ቻይና በኢትዮጵያ ለድርቅ ተጎጂዎች የሚውል 8 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ የሰብአዊ ደጋፍ አደረገች
    አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቻይና መንግስት የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት የሚያደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር 8 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ግምት ያለው የሰብአዊ ድጋፍ...
    0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares