0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMየኮሪያ መንግሥት ለኢትዮጵያ የፍጥነት መንገዶች ግንባታ ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታወቀ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicየደቡብ ኮሪያ መንግሥት በኢትዮጵያ እየተገነቡ ለሚገኙና ወደፊት እንደሚገነቡ ለሚታሰቡ የመንገድ መሠረተ ልማቶች ድጋፍ የመስጠት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡ በአዳዲስ መንገዶች ግንባታ ለመሳተፍ የኮሪያ መንግሥት ኩባንያ ከመንግሥት ጋር ድርድር ጀምሯል፡፡0 Comments 0 Shares
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMነዳጅ ድርጅት የአንድ ዓመት ነዳጅ ግዥ ውል ተፈራረመ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicየኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ለ2010/2011 በጀት ዓመት ፍጆታ የሚውል የነዳጅ አቅርቦት ስምምነት ትራፊጉራ ከተሰኘ የስዊዘርላንድ ኩባንያ ጋር ተፈራረመ፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከኩዌትና ሱዳን መንግሥታት ጋር በገባው ውል መሠረት አብዛኛውን ነዳጅ የሚገዛው ከሁለቱ አገሮች ሲሆን፣ የተቀረውን የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በየዓመቱ በሚያወጣው ዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅቶችን አወዳድሮ ይገዛል፡፡0 Comments 0 Shares
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMየዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ሊቀርቡ ባለመቻላቸው ዶ/ር መረራ ለብይን ተቀጠሩ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicዓቃቤ ሕግ እንዲከላከሉ ብይን ይሰጥልኝ ብሏል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 01/2009 አንቀጽ 12(1) ሥር የተደነገገውንና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ ዕርምጃ አፈጻጸም አንቀጽ 2(1)ን በመተላለፍ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማስወገድ ሙከራ ወንጀል የተከሰሱት ዶ/ር መረራ ጉዲና ለብይን ተቀጠሩ፡፡0 Comments 0 Shares
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMከ57 ዓመታት በኋላ የንግድ ሕግ ረቂቅ ማሻሻያ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀረበ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicበተደጋጋሚ ውድቅ የተደረገው የወንጀል ሥነ ሥርዓት ረቂቅ ሕግ በድጋሚ ቀርቧል ከ1952 ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ላይ የሚገኘውን የንግድ ሕግ የሚያሻሽል አዲስ ረቂቅ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን፣ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡ በተጨማሪም ከ1954 ዓ.ም. ጀምሮ በተግባር ላይ የቆየውንና ተሞክሮ በተደጋጋሚ ውድቅ ተደርጎ የነበረው የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕጉንም ለማሻሻል፣ ድጋሚ ማሻሻያ ረቂቅ ሕግ መቅረቡንም ዋና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ጌታቸው አምባዬ ረቡዕ ኅዳር 20 ቀን 2010 ዓ.ም. በተወካዮች ምክር ቤት የመሥሪያ ቤታቸውን የሩብ ዓመት ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ገልጸዋል፡፡0 Comments 0 Shares
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMከጂቡቲ ኢትዮጵያ ሊዘረጋ የታሰበው የነዳጅ መስመር ፕሮጀክት ታጠፈ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicኢትዮጵያ በከፍተኛ ወጪ ከጂቡቲ ወደብ ወደ መሀል አገር የምታስገባው የተጣራ የነዳጅ ውጤቶች ማስተላለፊያ ቧንቧ መስመር ፕሮጀክት እንደታጠፈ ታወቀ፡፡ ተቀማጭነቱ በደቡብ አፍሪካ የሆነው ብላክ ራይኖ የተባለ ኩባንያ ከጂቡቲ ወደብ አዋሽ አርባ የሚገኘው የነዳጅ ዴፖ የሚደርስ 550 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧ ለመዘርጋት የሚያስችል ዕቅድ፣ ለኢትዮጵያ መንግሥት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡0 Comments 0 Shares
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የተቀጠሩ ሠራተኞችን እመነጥራለሁ አለ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጭበርብረው የተቀጠሩ ሠራተኞችን ለመመንጠር አዲስ ዕቅድ አወጣ፡፡ የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በሁሉም መሥሪያ ቤቶች ይህንን የሚሠራ ኮሚቴ ያቋቋመ ሲሆን፣ በማዕከል ደረጃ ፖሊስና ፍትሕ ቢሮ ያሉበት ግብረ ኃይል አቋቁሟል፡፡ ቢሮው ሒደቱ የሚመራበትን መመርያ በማዘጋጀት በማዕከል፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ መዋቅሮች ከሚመለከታቸው ጋር ሲመክር ቆይቷል፡፡0 Comments 0 Shares
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMለ35 ቀናት ግምገማ ላይ የቆየው የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አዲስ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አዋቀረ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharicለ35 ቀናት በግምገማ ላይ የከረመው የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት (ትግራይ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴውን እንደገና በማዋቀር ተጠናቀቀ፡፡ ሐሙስ ኅዳር 21 ቀን 2010 ዓ.ም. ከአንድ ወር በላይ የፈጀ ስብሰባውን ያጠናቀቀው የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ዘጠኝ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን መርጧል፡፡ ባወጣው የአቋም መግለጫም ራሱ ላይ አካሂጃለሁ ያለውን ሥር ነቀል ግምገማ በዝርዝር አስታውቋል፡፡0 Comments 0 Shares