0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMእስራኤል በሊባኖስ ላይ ያካሄደችው ጥቃት ቀጠናዊ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯልእስራኤል ሰኞ እለት ሊባኖስ ውስጥ በሚገኙት የሂዝቦላህ ታጣቂዎች ላይ ባካሄደችው የአየር ድብደባ ቢያንስ 490 ሰዎች ሲገደሉ ከ1ሺህ 600 በላይ መቁሰላቸውን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። እስራኤል በአካሄደችው በዚህ ጥቃት ጦርነቱ በቀጠናው ሊስፋፋ ይችላል የሚል ስጋት እያየለ መሄዱን ጠቅሳ፣ የአሜሪካ ድምጿ ዘጋቢ ካትሪን ጂፕሰን ያደረሰችንን ዘገባ፣ ነው፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMኢትዮጵያ ከቁም እንስሳት ሃብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን ላኪዎችን የሚያበረታቱ አስራሮችን መተግበር እንደሚገባት ተገለጸለመጀመሪያ ጊዜ የቁም እንስሳት ወጪ ንግድ በባቡር ከአዳማ ወደ ጁቡቲ ማጓጓዝ መጀመሩን የኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊዎች በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ይህም የሃገሪቱን የወጭ ንግድ ግኝት ከፍ ለማድረግ እንደሚያስችል የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ ገልጸዋል፡፡ የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ሚልዮን ክብረት በበኩላቸው ሃገሪቱ ከቁም እንስሳት ሃብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን ላኪዎችን የሚያበረታቱ ተጨማሪ አስራሮችን መተግበር እንደሚገባት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMመንግሥት ያሳለፈውን ውሳኔ፣ የትራንስፖርት አሰሪዎች ፈደሬሽን ተቃወመውየትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የአገልግሎት ዘመናቸው ከ 30 አመት በላይ የሆኑ ተሽከርካሪዎች፣ ወደ ጅቡቲ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይሰጡ ያሳለፈው ውሳኔ ተቃውሞ ገጠመው፡፡ የኢትዮጵያ የትራንስፖርት አሰሪዎች ፈደሬሽን፣ መንግስት ከአንድ አመት በፊት ያወጣውን መመሪያ መሰረት በማድረግ፣ በቅርቡ ከ 30 አመት በላይ የሰሩ ተሽከርካሪዎች ድንበር ተሻጋሪ የጭነት አገልግሎት እንዳይሰጡ ማገዱን ገልፆ፣ ውሳኔው የተለያዩ ችግሮችን ስለሚያስከትል እንደገና ሊጤን...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COM"ዩናይትድ ስቴትስ ለአፍሪካ ሀገሮች አንድ ሚሊዮን የኤም ፖክስ ክትባት ትለግሳለች" ፕሬዚደንት ባይደንዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ሀገሮች የያዙት የጸረ ኤም ፖክስ ወረርሽኝ ትግል ለመደገፍ አንድ ሚሊዮን ክትባቶችን እና ቢያንስ የአምስት መቶ ሚሊዮን ዶላር እርዳታ መስጠቷን ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ዛሬ አስታወቁ። ዛሬ ማክሰኞ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባሰሙት ንግግር እርዳታውን ይፋ ያደረጉት ፕሬዚደንት ባይደን ሊሎች ሀገሮችም ተመሳሳይ እርዳታ እንዲያደርጉ ተማጽነዋል። "ኤምፖክስን ለመጋፈጥ ፈጥነን መንቀሳቀስ አለብን " ብለዋል ባይደን። የዓለም...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበኢትዮጵያ ከ9 ሺህ በላይ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታቸው ተገለፀባለፉት 6 ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኙ 10 ሺህ የሚጠጉ ስደተኞች ፋይዳ የተሰኘ ዲጂታል መታወቂያ እነደተሰጣቸው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር፣ በምህጻሩ ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር አስታውቋል። ዲጂታል መታወቂያው፣ ስደተኞች የተለያዩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የደኅንነት አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እንደሚያስችል ተቋሙ ገልጿል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰማኮ) ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ፣ተመዝግበው እውቅና ማግኘት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMባይደን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የመሰናበቻ ንግግር አደረጉየአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን በ79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጀት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ዛሬ ማክሰኞ ንግግር አድርገዋል። 20 ደቂቃ ያህል የፈጀው ንግግራቸው፣ የፕሬዝደንትነት ዘመናቸው ለሚያበቃው ባይደን ተመድን የመሰናበቻ ንግግር ተደርጎ ይቆጠራል። በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በዩክሬን እንዲሁም በአፍሪካ የሚካሄዱት ጦሮነቶች የንግግሮቻቸው ዋና መልዕክቶች ነበሩ።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMእስራኤል በሊባኖስ ባደረሰቻቸው ጥቃቶች የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ550 ማለፉ ተገለጸእስራኤል በሁለቱ ቀናት ባደረሰቻቸው የአየር ጥቃቶች 558 ሰዎች መገደላቸውን የሊባኖስ የጤና ባለሥልጣናት ተናገሩ። ዛሬ ማክሰኞ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ ላይ በተደጋጋሚ የአየር ድብደባ አካሂዳለች። ጥቃቶቹ ኢላማ ያደረጉት ወደሰሜናዊ እስራኤል ሮኬቶች የሚተኩሱትን ጨምሮ በርካታ የሄዝቦላ ተዋጊዎችን መሆኑን አመልክታለች። ሄዝቦላ በበኩሉ ዛሬ ማክሰኞ የእስራኤል ወታደራዊ ሠፈሮች ላይ ያነጣጠረ የሮኬት ጥቃት ማድረሱን አስታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ...0 Comments 0 Shares