0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMትረምፕ እና ሃሪስ ለመጀመሪያው ክርክራቸው እየተዘጋጁ ነውየዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ እጩዎች ዶናልድ ትራምፕ እና ካማላ ሃሪስ ሁለት ወራት ለቀረው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያተኩረውን የመጀመሪያ ክርክራቸውን ለማካሄድ የምርጫ ዘመቻዎቻቸው እየተዘጋጁ መሆናቸው ተዘገበ። የምርጫ ውድድሩን ሂደት የሚዳስሰውን ዘገባ ከዚህ ይከታተሉ።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበአማራ ክልል የደረሰው የመሬት መንሸራተት ያደረሰው ጉዳትበአማራ ክልል ምስራቃዊ አካባቢዎች ላይ የደረሰው የመሬት መንሸራተትና መስረግ አደጋ ከአንድ ሽህ ሄክታር በላይ በዘር የተሸፈነ እና የግጦሽ መሬት ከጥቅም ውጭ ማድረጉን በሰሜን እና ደቡብ ወሎ እንዲሁም በሰሜን ሸዋ ዞኖች የሚገኙ የየአካባቢዎቹ ባለሥልጣናት አስታወቁ፡፡ ባለስልጣናቱ እንዳስረዱት በአደጋው ስምንት ሽህ የሚሆኑ ሰዎች ተጎጅ ሲሆኑ አብዛኞቹ ለመፈናቀል ተዳርገዋል፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከክልሉ ከተሞች ነዋሪዎች ጋር የያዘው ውይይትከተለያዩ የክልሉ ከተሞች ነዋሪዎች ጋር ህዝባዊ ውይይት ማካሄድ የጀመሩት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ ውይይቱ አስተዳደሩ ያሉበትን ክፍተቶች ለማረምና አዎንታዊ ነገሮችን ለማስቀጠል እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል። አቶ ጌታቸው፣ ትላንት ማክሰኞ፣በዓዲግራት ከተማ በነበረው ውይይት ላይ ባደረጉት ገለጻ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በሚመሩት ሰዎች ላይ "ከፍተኛ የሆነ ስም የማጥፋት ሥራ ተፈጽሟል" ሲሉ ተችተዋል። በቅርቡ በተካሄደው 14ኛው የህወሓት ጉባኤ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMአቶ ታዬ ደንደአ የዋስ መብት ተከለከሉየፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀድሞው የሰላም ሚንስትር ድኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ያቀረቡትን የዋስትና መብት ጥያቄ ውድቅ አደረገ። አቃቤ ሕግ ካቀረበባቸዉ ክሶች ሁለቱ ውድቅ የተደረገላቸው አቶ ታዬ፣ በዛሬው ዕለት ስድስት ኪሎ ከሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ያቀረቡትን አቤቱታ ቀደም ሲል የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያሳለፈውን የፍርድ ውሳኔ በማፅናት ነው ጥያቄያቸውን ውድቅ ያደረገው።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየቻይና-አፍሪካ ትብብር ጉባኤ ተጀመረኢትዮጵያን ጨምሮ ከ50 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የታደሙበት የቻይና-አፍሪካ የትብብር ጉባዔ ዛሬ በቤጂንግ ተከፍቷል። ለሦስት ቀናት በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ላይ፣ እስከ አውሮፓውያኑ 2027 በሚኖረው የቻይና እና አፍሪካ ግንኙነት የትብብር ሰነዶች ላይ ውይይት ተደርጎ ስምምነት እንደሚፈረም ይጠበቃል፡፡ በጉባኤው ለመሳተፍ ቤጂንግ ከገቡ የአፍሪካ መሪዎች አንዱ የሆኑት፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ቻይና አበርክታለች ያሉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMሂዩማን ራይትስ ዋች “ሊባኖስና ቆጵሮስ ፍልሰተኞችን ወደ ሶሪያ መልሰው እያባረሩ ነው” አለዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶቶች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች የሊባኖስ ጦር እና በአቅራቢያው ቆጵሮስ የሚገኙ ባለሥልጣናት ፍልስተኞች ወደ አውሮፓ እንዳይደርሱ በማድረግ በጦርነት ወደ ታመሰችው ሶሪያ መልሰው በማባረር በጋራ እየሰሩ ነው ሲል ከሰሰ፡፡ የሊባኖስ ጦር በጀልባ ለመውጣት የሚሞክሩትን ሶሪያውያን ስደተኞችን “ ይዞ በመመለስ ወዲያውኑ ወደ ሶሪያ እንዳሚያባርራቸው” የመብት ተሟጋቹ ድርጅት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የባህር ዳርቻ ጠባቂዎችን ጨምሮ የቆጵሮስ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ኢላማ ባደረጉ የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻ በማካሄድ ልትወነጅል ተዘጋጅታለችየባይደን አስተዳደር ሩሲያን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይ ባነጣጠሩ የሃሰት መረጃ ቅስቀሳዎች ለመክሰስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ስለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሰዎች ተናገሩ፡፡ ከመግለጫው በፊት በይፋ መናገር ያልተፈቀደላቸው በመሆኑ ስማቸው ያልተገለጸ ሰዎችን ጠቅሶ አሶሴይትድ ፕሬስ እንደዘገበው የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሜሪክ ጋርላንድ ዛሬ ረቡዕ ስለጉዳዩ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የስለላ ተቋማት ቀደም ሲል ሩሲያ በምርጫው ውስጥ ጣልቃ ለመግባት...0 Comments 0 Shares