0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMኬንያ ውስጥ ተቆራርጠው ተጥለው በተገኙት የሰውነት አካላት ጉዳይ የተያዘው ተጠርጣሪ ከእስር አመለጠ42 ሴቶችን መግደሉን ያመነው እና ተቆራርጠው በተጣሉት የሰውነት አካላት ጉዳይ ‘እጁ አለበት’ ሲል በቁጥጥር ስር አውሎት የነበረው ተጠርጣሪ ከእስር ማምለጡን የኬንያ ፖሊስ አስታወቀ። ኮሊንስ ጁማሲ ካሉሻ በወንጀሉ ተጠርጥሮ የተያዘው መርማሪዎች ክስ ከመመስረታቸው አስቀድሞ ወንጀሉን እንዲያጣሩ ፍርድ ቤት ሰባት ተጨማሪ ቀናት ከፈቀደላቸው በኋላ ነው። ሆኖም የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊው እንዳስረዱት፤ ካሉሻ ከሌሎች 12 እስረኞች ጋር በመሆን ዛሬ ማለዳ ላይ የእስር...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMባይደን በፓርቲያቸው ጉባኤ ደማቅ አቀባበል ተደረላቸውበትላንቱ የዲሞክራቲክ ፓርቲያቸው ጉባኤ እጅግ ላቅ ያለ አክብሮት የተቸረ ንግግር ያሰሙት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፣ የዳግም ምርጫ ዘመቻቸውን አቋርጠው በምትካቸው ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሀሪስ እንዲወዳደሩ ያደረጉበት ውሳኔ ትኩስ የመነቃቃት ስሜት ፈጥሯል። ባይደን ዳግም ለመመረጥ ይዘውት የነበረውን ዘመቻ ገትተው ቦታውን ለሃሪስ እንዲለቁ በርካታ የፓርቲያቸው አመራሮች ግፊት ካደረጉባቸው ሳምንታት በኋላ ትላንትናት ምሽት ወደ ጉባኤው መድረክ ብቅ ሲሉ ከፓርቲያቸው አባላት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየኤምሬትሱ ኩባንያ አሚያ ፓወር በ628 ሚሊዮን ዶላር በኢትዮጵያ የነፋስ ኀይል ሊያመርት ነውየተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ኩባንያ የኾነው አሚያ ፓወር፣ በኢትዮጵያ በ628 ሚሊዮን ዶላር የነፋስ ኀይል ለማመንጨት፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ ከመንግሥት ጋራ ስምምነት ተፈራረመ፡፡ አሚያ ፓወር፥ በሶማሊ ክልል፣ በአይሻ - አንድ የነፋስ ኀይል ማመንጫ ጣቢያ፣ 300 ሜጋ ዋት ኃይል በማልማት ለ25 ዓመታት ለመንግሥት እንደሚያቀርብ፣ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ የግል ባለሀብቶች በኀይል ልማት ዘርፍ እንዲሰማሩ፣ ከስድስት ዓመት በፊት፣ የመንግሥት እና የግል...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን አቶ ጌታቸው ረዳን ማገዱን አስታወቀበሁለት ቡድኖች ተከፍሎ እየተወዛገበ ከሚገኘው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራር ውስጥ፣ ላለፉት ሰባት ቀናት በመቐለ የሰማዕታት ሐወልት አዳራሽ ሲያካሒድ የቆየውን ጉባኤ ዛሬ ሰኞ ያጠናቀቀው በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ቡድን፣ አቶ ጌታቸው ረዳን ከፓርቲው አባልነት ማገዱን፣ከፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበርነትም ማንሳቱን አስታውቋል። በጉባኤው ያልተሳተፉ ሌሎች አመራሮችንም ከፓርቲ አባልነት ማገዱን ጠቁሟል። ጉባኤው፣ ዶክተር ደብረ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMጣልያን ውስጥ አንድ ቅንጡ ጀልባ ተገልብጣ አንድ ሰው ሲሞት 6ቱ ጠፍተዋልበጣልያን ግዛት ሲሲሊ ፓሌርሞ ወደብ አቅራቢያ ከባህር ስትቀዝፍ የነበረች አንዲት ቅንጡ ጀልባ ዛሬ ሰኞ በመገልበጧ በውስጧ ከነበሩ ቱሪስቶች መካከል አንድ ሰው ሲሞት 6 ሰዎች የገቡበት አልታወቀም፡፡ የነፍስ አንድ ሠራተኞች የአንድ ዓመት ህጻንን ጨምሮ የ15 ተሳፋሪዎችን ህይወት ማትረፍ እንደቻሉ ባለሥልጣናት ተናግረዋል፡፡ የነፍስ አድን ሠራተኞች ጀልባዪቱን ያወጧት ከባህሩ 50 ሜትር ጠልቃ ከገባችበት ባህር መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ከፖርቲሴሎ ወደብ ከንጋቱ 11...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየኬንያ መንግሥት አንዳንድ የግብር እርምጃዎችን ወደነበሩበት ሊመልስ ነውየኬንያ መንግስት በቅርቡ በተቀሰቀሰው ተቃውሞና ሁከት ሳቢያ አስቀርቷቸው ከነበሩት የግብር (ታክስ) ህጎች ውስጥ አንዳንዶቹን መልሶ ተግባራዊ በማድረግ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አስታወቁ፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ ጆን ምባዲ ትላንት እሁድ ሲቲዝን ቲቪ ለተባለ አንድ የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ እንደተናገሩት መንግስት ወደ 150 ቢሊዮን ሽልንግ (1.2 ቢሊዮን ዶላር) ለመሰብሰብ እንዲችል ወደ 49 የሚጠጉ የታክስ እርምጃዎችን ተግባራዊ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየዲሞክራቲክ ፓርቲ ብሔራዊ ጉባኤ ዛሬ ይጀምራልዛሬ ምሽት በሚጀምረው የዲሞክራቲክ ፓርቲ ብሔራዊ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ከየክፍለ ግዛቱ የተውጣጡ በሺሕ የሚቆጠሩ የፓርቲው ተወካዮች በቺካጎ ከተማ ተገኝተዋል። ለአራት ቀናት የሚቆየው ብሔራዊ ጉባኤ፣ የፓርቲው ፕሬዝደንታዊ እጩ ካመላ ሄሪስ እና እጩ ምክትል ፕሬዝደንት ቲም ዋልዝ፣ የቀድሞው ፕሬዝደንቶች ባራክ ኦባማ እና ቢል ክሊንተን እንዲሁም ታዋቂ የፓርቲው ዓባላት የሚያደርጉትን ንግግር ያደምጣል። ጉባኤው በዛሬው የመጀመሪያ ቀን ውሎ የፕሬዝደንት ጆ ባይደንን...0 Comments 0 Shares