ጣልያን ውስጥ አንድ ቅንጡ ጀልባ ተገልብጣ አንድ ሰው ሲሞት 6ቱ ጠፍተዋል
በጣልያን ግዛት ሲሲሊ ፓሌርሞ ወደብ አቅራቢያ ከባህር ስትቀዝፍ የነበረች አንዲት ቅንጡ ጀልባ ዛሬ ሰኞ በመገልበጧ በውስጧ ከነበሩ ቱሪስቶች መካከል አንድ ሰው ሲሞት 6 ሰዎች የገቡበት አልታወቀም፡፡
የነፍስ አንድ ሠራተኞች የአንድ ዓመት ህጻንን ጨምሮ የ15 ተሳፋሪዎችን ህይወት ማትረፍ እንደቻሉ ባለሥልጣናት ተናግረዋል፡፡
የነፍስ አድን ሠራተኞች ጀልባዪቱን ያወጧት ከባህሩ 50 ሜትር ጠልቃ ከገባችበት ባህር መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ከፖርቲሴሎ ወደብ ከንጋቱ 11...