ባይደን በፓርቲያቸው ጉባኤ ደማቅ አቀባበል ተደረላቸው
በትላንቱ የዲሞክራቲክ ፓርቲያቸው ጉባኤ እጅግ ላቅ ያለ አክብሮት የተቸረ ንግግር ያሰሙት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፣ የዳግም ምርጫ ዘመቻቸውን አቋርጠው በምትካቸው ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሀሪስ እንዲወዳደሩ ያደረጉበት ውሳኔ ትኩስ የመነቃቃት ስሜት ፈጥሯል። ባይደን ዳግም ለመመረጥ ይዘውት የነበረውን ዘመቻ ገትተው ቦታውን ለሃሪስ እንዲለቁ በርካታ የፓርቲያቸው አመራሮች ግፊት ካደረጉባቸው ሳምንታት በኋላ ትላንትናት ምሽት ወደ ጉባኤው መድረክ ብቅ ሲሉ ከፓርቲያቸው አባላት...