0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
-
ኢማኑኤል አዴባዮር በህይወቱ ፀፀት የሆነበትን ውሳኔ ይፋ አደረገ
ሪያል ማድሪድን ጨምሮ በአርሰናል ፣ በማንችስተር ሲቲና ቶተንሐም ቆይታ ማድረግ የቻለው ቶጎአዊ የፊት አጥቂ ኢማኑኤል አዴባዮር በእግር ኳስ ህይወቱ ከሚያስፀፅቱት ውሳኔዎች ዋነኛው በ2016 ለክሪስታል ፓላስ ለመጫወት መስማማቱ መሆኑን ገልጿል፡፡ . ተጫዋቹ በወቅቱ ክለብ አልባ የነበረ በመሆኑ የቀረበለትን የፈርምልን ጥያቄ ሳያቅማማ የተቀበለ ቢሆንም በመጀመሪያዎቹ 15 ጨዋታዎች አንድ ጎል ብቻ ካስቆጠረ በኋላ ወደተጠባባቂ ወንበር ወርዶ ውሉን ለመጨረስ ተገዷል፡፡. ተጫዋቹ ለ ለኪፕ እንደተናገረው “በእንግሊዝ ከታላላቅ ክለቦች ጋር መልካም ጊዜያትን አሳልፌአለሁ ፤ እኔና ቤተሰቤ ደስተኛ ነበርን፡፡ የሰራሁት ብቸኛ ስህተት ለፓላስ ለመጫወት መስማማቴ ነው፡፡ ይህን ያደረኩት ለኔ ሰዎች ስል ነው፡፡ ሁሌም ‘ወደሜዳ ተመለስ እንጂ!’ ይሉኝ ነበር፡፡ የጨዋታ ዘመኔ መጥፎ ውሳኔ ነበር”ብሏል፡፡ ተጫዋቹ ወደቱርክ በማቅናት ለባሳክሺር ከፈረመ በኋላ ወደቀድሞ ብቃቱ የተመለሰ ሲሆን ክለቡን ለቱርክ ዋንጫ ፍፃሜ ማድረስ ችሏል፡፡ አዴባዮር ጨምሮም የቱርክ ቆይታው እንደተመቸውና ወደሌላ ክለብ የመዘዋወር ዕቅድ እንደሌለው አሳውቋል፡፡ኢማኑኤል አዴባዮር በህይወቱ ፀፀት የሆነበትን ውሳኔ ይፋ አደረገ ሪያል ማድሪድን ጨምሮ በአርሰናል ፣ በማንችስተር ሲቲና ቶተንሐም ቆይታ ማድረግ የቻለው ቶጎአዊ የፊት አጥቂ ኢማኑኤል አዴባዮር በእግር ኳስ ህይወቱ ከሚያስፀፅቱት ውሳኔዎች ዋነኛው በ2016 ለክሪስታል ፓላስ ለመጫወት መስማማቱ መሆኑን ገልጿል፡፡ . ተጫዋቹ በወቅቱ ክለብ አልባ የነበረ በመሆኑ የቀረበለትን የፈርምልን ጥያቄ ሳያቅማማ የተቀበለ ቢሆንም በመጀመሪያዎቹ 15 ጨዋታዎች አንድ ጎል ብቻ ካስቆጠረ በኋላ ወደተጠባባቂ ወንበር ወርዶ ውሉን ለመጨረስ ተገዷል፡፡. ተጫዋቹ ለ ለኪፕ እንደተናገረው “በእንግሊዝ ከታላላቅ ክለቦች ጋር መልካም ጊዜያትን አሳልፌአለሁ ፤ እኔና ቤተሰቤ ደስተኛ ነበርን፡፡ የሰራሁት ብቸኛ ስህተት ለፓላስ ለመጫወት መስማማቴ ነው፡፡ ይህን ያደረኩት ለኔ ሰዎች ስል ነው፡፡ ሁሌም ‘ወደሜዳ ተመለስ እንጂ!’ ይሉኝ ነበር፡፡ የጨዋታ ዘመኔ መጥፎ ውሳኔ ነበር”ብሏል፡፡ ተጫዋቹ ወደቱርክ በማቅናት ለባሳክሺር ከፈረመ በኋላ ወደቀድሞ ብቃቱ የተመለሰ ሲሆን ክለቡን ለቱርክ ዋንጫ ፍፃሜ ማድረስ ችሏል፡፡ አዴባዮር ጨምሮም የቱርክ ቆይታው እንደተመቸውና ወደሌላ ክለብ የመዘዋወር ዕቅድ እንደሌለው አሳውቋል፡፡0 Comments 0 Shares -
የአርሰናሉ ተከላካይ ሌዮሬንት ኮስሌኒይ ወደ ማርሴ አይዘዋወርም::
ሌዮሬንት ኮስሌኒይ በአርሰናል ውስጥ መቆየቱ ጥሩ ስሜት እንዲሰማው እንዳደረገው ተቀብሏል ነገር ግን የልጅነት ክለቡ ማርሴ የእንውሰድህ ጥያቄ ቢያቀርብለት አይሆንም ለማለት እንደሚቸገርና ምክንያታዊ እንደሆነ ተናግሯል ጊዜው አልታወቀም እንጂ ሊሆንም እንደሚችልም ጭምር:: ይህ ፈረንሳዊ በ 2010 ባልተገለፀ የዝውውር ሂሳብ ከሎሬንት መድፈኞቹን ከተቀላቀለ ጀምሮ ለቡድኑ የኃላ መስመር የልብ ትርታ ሆኗል:: አሁን ላይ በአሜሪካው ቢሊየነር የበጀት ድጋፍ ስር የሚገኘው ክለብ ማርሴ ያለውን የቡድን ጥልቀት በጥንቃቄ በመገምገም በቀጣዩ የውድድር ዘመን ለሚገጥመው ፋክክር ከመሪዎቹ ተርታ ለመሰለፍ ይህንን የ 31 ዓመት ፈረንሳዊ ዒላማ አድርጎ ብቅ ብሏል:: ኮስሌኒይ ግን ወደ ቬሌድሮም ስታዲየም ያመራል የሚባለውን ተቃውማል:: ኮስሌኒይ ለቴሌፋት እንደተናገረው ” አሁንም ድረስ ከአርሰናል ጋር ውል አለኝ እንዲያውም ባለፈው ሕዳር ወር እስከ 2020 የሚያቆየኝን ፊርማ አስቀምጫለሁ:: ” በአርሰናል ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው:: ይሄ ሁልግዜም የምናገረው ነው በልጅነቴ የማርሴ ደጋፊ ነበርኩ:: እንደማርሴ ባለ ታሪካዊ ክለብ መፈለግ ጥሩ ነው:: ነገር ግን እኔ ፊርማዬን አኖራለሁ??? አላውቅም!!! በአርሰናል በጣም ደስተኛ ነኝ ” ሲል ተናግሯል:: የቡድን አጋሩ ኦሊቪዬ ዢሩ እና በቶተነሀም የተገፋው ሙሳ ሲሶኮ በቅርብ ቀናት በዝውውር ገበያው ስማቸው ከፈረንሳዩ ክለብ ጋር የተያያዘ ተጫዋቾች ናቸው::የአርሰናሉ ተከላካይ ሌዮሬንት ኮስሌኒይ ወደ ማርሴ አይዘዋወርም:: ሌዮሬንት ኮስሌኒይ በአርሰናል ውስጥ መቆየቱ ጥሩ ስሜት እንዲሰማው እንዳደረገው ተቀብሏል ነገር ግን የልጅነት ክለቡ ማርሴ የእንውሰድህ ጥያቄ ቢያቀርብለት አይሆንም ለማለት እንደሚቸገርና ምክንያታዊ እንደሆነ ተናግሯል ጊዜው አልታወቀም እንጂ ሊሆንም እንደሚችልም ጭምር:: ይህ ፈረንሳዊ በ 2010 ባልተገለፀ የዝውውር ሂሳብ ከሎሬንት መድፈኞቹን ከተቀላቀለ ጀምሮ ለቡድኑ የኃላ መስመር የልብ ትርታ ሆኗል:: አሁን ላይ በአሜሪካው ቢሊየነር የበጀት ድጋፍ ስር የሚገኘው ክለብ ማርሴ ያለውን የቡድን ጥልቀት በጥንቃቄ በመገምገም በቀጣዩ የውድድር ዘመን ለሚገጥመው ፋክክር ከመሪዎቹ ተርታ ለመሰለፍ ይህንን የ 31 ዓመት ፈረንሳዊ ዒላማ አድርጎ ብቅ ብሏል:: ኮስሌኒይ ግን ወደ ቬሌድሮም ስታዲየም ያመራል የሚባለውን ተቃውማል:: ኮስሌኒይ ለቴሌፋት እንደተናገረው ” አሁንም ድረስ ከአርሰናል ጋር ውል አለኝ እንዲያውም ባለፈው ሕዳር ወር እስከ 2020 የሚያቆየኝን ፊርማ አስቀምጫለሁ:: ” በአርሰናል ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው:: ይሄ ሁልግዜም የምናገረው ነው በልጅነቴ የማርሴ ደጋፊ ነበርኩ:: እንደማርሴ ባለ ታሪካዊ ክለብ መፈለግ ጥሩ ነው:: ነገር ግን እኔ ፊርማዬን አኖራለሁ??? አላውቅም!!! በአርሰናል በጣም ደስተኛ ነኝ ” ሲል ተናግሯል:: የቡድን አጋሩ ኦሊቪዬ ዢሩ እና በቶተነሀም የተገፋው ሙሳ ሲሶኮ በቅርብ ቀናት በዝውውር ገበያው ስማቸው ከፈረንሳዩ ክለብ ጋር የተያያዘ ተጫዋቾች ናቸው::0 Comments 0 Shares -
የቀድሞው የኤሲ ሚላን ፣ ሮማ ፣ ጁቬንቱስና ሪያልማድሪድ አሰልጣኝ ውጤታማው ፋቢዮ ካፔሎ ወደክለብ ማሰልጠን ስራቸው በመመለስ የቻይናው ክለብ ጂያንሱ ሰኒንግ አሰልጣኝ ሆነዋል፡፡ በ2007 ሪያል ማድሪድን ከለቀቁ በኋላ ከክለብ አሰልጣኝነት ርቀው የቆዩት ካፔሎ በበሔራዊ ቡድን ደረጃ የእንግሊዝና የሩሲያን ብሔራዊ ቡድን ሲያሰለጥኑ ቆይተዋል፡፡ በ 2015 ከሩሲያ ኃላፊነታቸው የለቀቁት አሰልጣኙ እስከአሁን ስራ ፈትተው የሰነበቱ ቢሆንም አሁን ግን በረብጣ ሚልዮን ዶላሮች የበለፀገው የቻይና ሱፐር ሊግ ማረፊያቸው ሆኗል፡፡ የጣልያናዊውን ግልጋሎት ለማግኘት የተስማማው ሰኒንግ በ2016 የውድድር ዘመን በሊጉ ሁለተኛ ሆኖ መጨረስ ችሎ የነበረ ቢሆንም በዘንድሮው የውድድር ዘመን ግን በወራጅ ቀጠናው ውስጥ እየዳከረ ይገኛል፡፡ የስምምነት ስርአቱን ተከትሎ የክለቡ ይፋዊ መግለጫ የተሰጠ ሲሆን”አሰልጣኝ ካፔሎን ለማስፈረም የተደረሰው ውሳኔ የክለቡ የለውጥና የዕድገት ፍላጎት እንቅስቃሴ አካል ነው” የሚል ቃል ይገኝበታል፡፡ በተጨማሪም”ክለቡን ከመምራት በተጓዳኝ በክለብ አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ዘመናዊ አሰራርና የተሻሉ ሃሳቦችን ማስረጽ ሌላኛው ኃላፊነቱ ነው ፤ በዚህም የኛ ክለብ ላይ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው የቻይና እግር ኳስ ላይ ለውጥ መፍጠር እንችላለን” ይላል፡፡ ጣልያናዊው ቆፍጣና በልዕልና ዘመናቸው አምስት የሴሪ አ ፣ ሁለት የላሊጋና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ክብርን በማግኘት ደማቅ ታሪክን ፅፈዋልየቀድሞው የኤሲ ሚላን ፣ ሮማ ፣ ጁቬንቱስና ሪያልማድሪድ አሰልጣኝ ውጤታማው ፋቢዮ ካፔሎ ወደክለብ ማሰልጠን ስራቸው በመመለስ የቻይናው ክለብ ጂያንሱ ሰኒንግ አሰልጣኝ ሆነዋል፡፡ በ2007 ሪያል ማድሪድን ከለቀቁ በኋላ ከክለብ አሰልጣኝነት ርቀው የቆዩት ካፔሎ በበሔራዊ ቡድን ደረጃ የእንግሊዝና የሩሲያን ብሔራዊ ቡድን ሲያሰለጥኑ ቆይተዋል፡፡ በ 2015 ከሩሲያ ኃላፊነታቸው የለቀቁት አሰልጣኙ እስከአሁን ስራ ፈትተው የሰነበቱ ቢሆንም አሁን ግን በረብጣ ሚልዮን ዶላሮች የበለፀገው የቻይና ሱፐር ሊግ ማረፊያቸው ሆኗል፡፡ የጣልያናዊውን ግልጋሎት ለማግኘት የተስማማው ሰኒንግ በ2016 የውድድር ዘመን በሊጉ ሁለተኛ ሆኖ መጨረስ ችሎ የነበረ ቢሆንም በዘንድሮው የውድድር ዘመን ግን በወራጅ ቀጠናው ውስጥ እየዳከረ ይገኛል፡፡ የስምምነት ስርአቱን ተከትሎ የክለቡ ይፋዊ መግለጫ የተሰጠ ሲሆን”አሰልጣኝ ካፔሎን ለማስፈረም የተደረሰው ውሳኔ የክለቡ የለውጥና የዕድገት ፍላጎት እንቅስቃሴ አካል ነው” የሚል ቃል ይገኝበታል፡፡ በተጨማሪም”ክለቡን ከመምራት በተጓዳኝ በክለብ አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ዘመናዊ አሰራርና የተሻሉ ሃሳቦችን ማስረጽ ሌላኛው ኃላፊነቱ ነው ፤ በዚህም የኛ ክለብ ላይ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው የቻይና እግር ኳስ ላይ ለውጥ መፍጠር እንችላለን” ይላል፡፡ ጣልያናዊው ቆፍጣና በልዕልና ዘመናቸው አምስት የሴሪ አ ፣ ሁለት የላሊጋና አንድ የሻምፒዮንስ ሊግ ክብርን በማግኘት ደማቅ ታሪክን ፅፈዋል0 Comments 0 Shares
-
“የአሻንቲ ህዝብ ለቡድኑ ጠንካራ ፀሎት አድርጓል ከአላህ ጋር ኢትዮጵያን ከአምስት ጎል ባላነሰ ውጤት እናሸንፋለን” – ሼህ ሀሩን አብዱል ሙሚን
የጋናዋ አሻንቲ ግዛት የእስልምና መሪ የሆኑት ሼህ ሀሩን አብዱል ሙሚን የአካባቢው የእስልምና ተከታዮች ለብሔራዊ ብድኑ ፀሎት እንዳደረጉና በፈጣሪ እርዳታ ሀገራቸው ጨዋታውን ከአምስት ጎል ባላነሰ ውጤት እንደምታሸንፍ ተናግረዋል። ሼሁ ከፀሎት በኋላ በኩማሲ መስኪድ ለተገኙት የቡድኑ ተጫዋቾች ባስተላለፉት መልዕክት ላይ ለብሔራዊ ቡድኑ ተገቢው ፀሎት መደረጉንና ከፈጣሪ ጋር ሀገራቸው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ተሳትፎዋን በድል እንደምትጀምር ያላቸውን በራስ መተማመን አጉልተው አሳይተዋል። በዚህ በኩማሲ መስኪድ በተደረገው የፀሎት ስነስርአት ላይ ሁለቱ ወንድማማቾች አንድሬ እና ጆርዳን አዩ፣ ረሺድ ሱማይላና አብዱል መጂድ ዋሪስ አይነት የቡድኑ ኮከቦች ተካፋይ ነበሩ። ከቡድኑ ተጫዋቾች በተጨማሪ የቡድኑ ምክትል አሰልጣኝ ኢብራሂም አንያራስ ታንኮ እና የህዝብ ግንኙነቱ ኢብራሂም ሳኔ ዳራ በፀሎቱ ተካፍለዋል። ከዛሬ ምሽቱ ትንቅንቅ በፊት ብዙዎች የማሸነፉን ግምት ለጥቋቁሮቹ ኮከቦች የሰጡ ቢሆንም ዋልያዎቹ በተሰጣቸው ያነሰ ግምት እንደማይደናገጡና በጨዋታው ላይ ውጤት ለማግኘት የተቻላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉ እየገለፁ ይገኛል። የቡድኑ አሰልጣኝ አሸናፊ ከበደ ከአንድ የጋና ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ “እናውቃለን ጋና ጠንካራ ቡድን ነው። ነገርግን እኛ እነሱን ስንገጥም የምናስደምምበት የራሳችን እቅድ አለን።” ሲሉ ተጋጣሚያቸው ጠንካራ ቢሆንም ለጨዋታው ዝግጁ እንደሆኑ አውስተዋል። ጋና ከ 1963 የአፍሪካ ዋንጫ ጀምሮ ዋሊያዎቹን ለሶስት ጊዜያት የገጠመች ሲሆን በሁለቱ ስታሸንፍ በአንዱ ሽንፈት ቀምሳለች። የሁለቱ ቡድኖች የመጨረሻ የቅርብ ጊዜ ግንኙነት በ 2014 ጋና 1-0 ያሸነፈችበት የቻን ውድድር መሆኑ ይታወሳል።“የአሻንቲ ህዝብ ለቡድኑ ጠንካራ ፀሎት አድርጓል ከአላህ ጋር ኢትዮጵያን ከአምስት ጎል ባላነሰ ውጤት እናሸንፋለን” – ሼህ ሀሩን አብዱል ሙሚን የጋናዋ አሻንቲ ግዛት የእስልምና መሪ የሆኑት ሼህ ሀሩን አብዱል ሙሚን የአካባቢው የእስልምና ተከታዮች ለብሔራዊ ብድኑ ፀሎት እንዳደረጉና በፈጣሪ እርዳታ ሀገራቸው ጨዋታውን ከአምስት ጎል ባላነሰ ውጤት እንደምታሸንፍ ተናግረዋል። ሼሁ ከፀሎት በኋላ በኩማሲ መስኪድ ለተገኙት የቡድኑ ተጫዋቾች ባስተላለፉት መልዕክት ላይ ለብሔራዊ ቡድኑ ተገቢው ፀሎት መደረጉንና ከፈጣሪ ጋር ሀገራቸው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ተሳትፎዋን በድል እንደምትጀምር ያላቸውን በራስ መተማመን አጉልተው አሳይተዋል። በዚህ በኩማሲ መስኪድ በተደረገው የፀሎት ስነስርአት ላይ ሁለቱ ወንድማማቾች አንድሬ እና ጆርዳን አዩ፣ ረሺድ ሱማይላና አብዱል መጂድ ዋሪስ አይነት የቡድኑ ኮከቦች ተካፋይ ነበሩ። ከቡድኑ ተጫዋቾች በተጨማሪ የቡድኑ ምክትል አሰልጣኝ ኢብራሂም አንያራስ ታንኮ እና የህዝብ ግንኙነቱ ኢብራሂም ሳኔ ዳራ በፀሎቱ ተካፍለዋል። ከዛሬ ምሽቱ ትንቅንቅ በፊት ብዙዎች የማሸነፉን ግምት ለጥቋቁሮቹ ኮከቦች የሰጡ ቢሆንም ዋልያዎቹ በተሰጣቸው ያነሰ ግምት እንደማይደናገጡና በጨዋታው ላይ ውጤት ለማግኘት የተቻላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉ እየገለፁ ይገኛል። የቡድኑ አሰልጣኝ አሸናፊ ከበደ ከአንድ የጋና ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ “እናውቃለን ጋና ጠንካራ ቡድን ነው። ነገርግን እኛ እነሱን ስንገጥም የምናስደምምበት የራሳችን እቅድ አለን።” ሲሉ ተጋጣሚያቸው ጠንካራ ቢሆንም ለጨዋታው ዝግጁ እንደሆኑ አውስተዋል። ጋና ከ 1963 የአፍሪካ ዋንጫ ጀምሮ ዋሊያዎቹን ለሶስት ጊዜያት የገጠመች ሲሆን በሁለቱ ስታሸንፍ በአንዱ ሽንፈት ቀምሳለች። የሁለቱ ቡድኖች የመጨረሻ የቅርብ ጊዜ ግንኙነት በ 2014 ጋና 1-0 ያሸነፈችበት የቻን ውድድር መሆኑ ይታወሳል።0 Comments 0 Shares -
Ghana 5-0 Ethiopia (CAN 2019 Qualifiers) - All Goals & Highlights 11/06/2017
Ghana 5-0 Ethiopia (CAN 2019 Qualifiers) - All Goals & Highlights 11/06/2017
0 Comments 0 Shares -