• ሪያድ ማህሬዝ ስለ አርሰን ዌንገር አድናቆት እና ስለ ቀጣዩ የሌስተር ቆይታው ይናገራል፡፡

    አልጄሪያዊው የሌስተር ሲቲው ተጫዋች ሪያድ ማህሬዝ ትላንት ምሽት ከ አል ሄዳፍ ቴሌቭዥን ጋር ባደረገው አጠር ያለ ቆይታ ስለ ሌስተር ቀጣይ ቆይተው እና ስለ አርሰን ዌንገር አድናቆት ምላሽ ሰጥቷል፡፡

    ተጫዋቹ ስለ ሌስተር ሲቲ ቀጣይ ቆይታው ” ባለፈው ዓመት ከክለቡ ሊቀመንበር ጋር አንድ ዓመት ከቆየሁ በኋላ ክለቡን መለቀቅ እንደምችል ተስማምተናል እናም አሁን ላይ ክለቡን ለመልቀቅ ትክክለኛው ሰዓት እንደሆነ ይሰማኛል ”

    ” በዚህ ክለብ ብዙ ልምዶችን አግንቻለሁ ፡፡ የ ፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ሆኜ የአመቱ ኮኮብ ተብያለሁ ፡፡በአውሮፓ መድረክም መጫወት ችያለሁ ስለዚህ አሁን ትክክለኛው ሰዓት ነው፡፡ እኔም ክለቡም በዚህ ነገር የምንስማማ ይመስለኛል ፡፡ ነገር ግን በእነደዚህ አይነት ጉዳይ ላይ እጄን ማስገባት አልፈልግም ሁሉንም ግዜ ይፈታዋል ”

    ብዙ ክለቦች እሱን ስለመፈለጋቸው ” ብዙ ክለቦች ፍላጎት አሳይተዋል ነገር ግን አሁን ከእዚህ ክለብ ጋር ተነጋግሪያለሁ ማለት አልችልም ለምን አሁንም የሌስተር ተጫዋች ነኝ ፡፡ መሄድ ካለብኝ እሄዳለሁ መቆየት ካለብኝም እንደዛው ስለዚህ አብረን የምናየው ይሆናል ፡፡

    ስለ አርሰን ዌንገር አድናቆት

    “በዚህ አለም ላይ ካሉ አሰልጣኞች መካከል ታላቅ በሆነ አሰልጣኝ እንደዚህ አይነት አድናቆት ማግኘት ለእኔ ክብር ነው ነገር ግን ምንም የተፈጠረ ነገር የለም “
    ሪያድ ማህሬዝ ስለ አርሰን ዌንገር አድናቆት እና ስለ ቀጣዩ የሌስተር ቆይታው ይናገራል፡፡ አልጄሪያዊው የሌስተር ሲቲው ተጫዋች ሪያድ ማህሬዝ ትላንት ምሽት ከ አል ሄዳፍ ቴሌቭዥን ጋር ባደረገው አጠር ያለ ቆይታ ስለ ሌስተር ቀጣይ ቆይተው እና ስለ አርሰን ዌንገር አድናቆት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ተጫዋቹ ስለ ሌስተር ሲቲ ቀጣይ ቆይታው ” ባለፈው ዓመት ከክለቡ ሊቀመንበር ጋር አንድ ዓመት ከቆየሁ በኋላ ክለቡን መለቀቅ እንደምችል ተስማምተናል እናም አሁን ላይ ክለቡን ለመልቀቅ ትክክለኛው ሰዓት እንደሆነ ይሰማኛል ” ” በዚህ ክለብ ብዙ ልምዶችን አግንቻለሁ ፡፡ የ ፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ሆኜ የአመቱ ኮኮብ ተብያለሁ ፡፡በአውሮፓ መድረክም መጫወት ችያለሁ ስለዚህ አሁን ትክክለኛው ሰዓት ነው፡፡ እኔም ክለቡም በዚህ ነገር የምንስማማ ይመስለኛል ፡፡ ነገር ግን በእነደዚህ አይነት ጉዳይ ላይ እጄን ማስገባት አልፈልግም ሁሉንም ግዜ ይፈታዋል ” ብዙ ክለቦች እሱን ስለመፈለጋቸው ” ብዙ ክለቦች ፍላጎት አሳይተዋል ነገር ግን አሁን ከእዚህ ክለብ ጋር ተነጋግሪያለሁ ማለት አልችልም ለምን አሁንም የሌስተር ተጫዋች ነኝ ፡፡ መሄድ ካለብኝ እሄዳለሁ መቆየት ካለብኝም እንደዛው ስለዚህ አብረን የምናየው ይሆናል ፡፡ ስለ አርሰን ዌንገር አድናቆት “በዚህ አለም ላይ ካሉ አሰልጣኞች መካከል ታላቅ በሆነ አሰልጣኝ እንደዚህ አይነት አድናቆት ማግኘት ለእኔ ክብር ነው ነገር ግን ምንም የተፈጠረ ነገር የለም “
    0 Comments 0 Shares
  • ዝላታን ኢብራሂሞቪችን የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ሁሌም እንዲያስታውሱት የሚያደርጉ 5 ነገሮች

    በአንድ የውድድር ዘመን 28 ጎሎችን በሁሉም ውድድሮች በማስቆጠር በርካቶችን ያስገረመው ዝላታን ኢብራሂሞቪች የደረሰበት ከባድ የጉልበት ጉዳት በቀጣይ አመት በቲያትር ኦፍ ድሪምስ የዩናይትድ ደጋፊያን እንዳይመለከቱት አድርጓል፡፡ ተከታዩ ጽሁፍም ስዊዲናዊው አጥቂ ባሳለፍነው አመት በዩናይትድ ቤት ያደረጋቸውን እና በደጋፊዎች ዘንድም እንዳይረሳ የሚያደርጉትን 5 ጉዳዩች ያስመለክተናል፡፡


    አለም ሆይ ቀጣይ ክለቤ ማንችስተር ዩናይትድ እንደሆነ እወቅልኝ ሲል የዩናይትድ ተጫዋች መሆኑን በይፋ ለአለም ባሳወቀ በአመቱ ቀያይ ሰይጣኖቹ እና ስዊዲናዊው ተለያይተዋል፡፡ የመጀመሪያውን የክለቡን ጨዋታውን ባደረገበት የስዊዲኑ ስቶኮልምም የኢሮፓ ሊግ ዋንጫን ከፍ በማድረግ በድል ቀያይ ሰይጣኖቹን ተሰናብቷል፡፡ እድሜው ከ30 በላይ ከሆነ በኋላ እያደር እንደ ወይን የጣፈጠው ስዊዲናዊው አጥቂ ከ250 በላይ ግቦችን ባለፉት 5 አመታት ከመረብ ማገናኘት ችሏል፡፡

    በኮምዩኒቲ ሺልድ ሌሲስተር ሲቲ ላይ ያስቆጠራት ወሳኝ ግብ

    በርካቶች ሊጉን ሲቀላቀል በዚህ እድሜው ቢሉም ስዊዲናዊው ግን በርካቶችን ዝም ማሰኘት የቻለው ገና ከወዲሁ ነበር፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ የኤፍ ኤካፕ አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ በእንግሊዝ ኮምዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ከሊጉ አሸናፊ ሌስተር ሲቲ ጋር ባደረገው ጨዋታ ዩናይትድን ባለድል ያደረገች ወሳኝ ግብ ጨዋታው መገበዳጃ ሰአት ላይ በጭንቅላቱ ገጭቶ ማስቆጠሩን ተከትሎ ቀያይ ሰይጣኖቹን ከአመታት በኋላ የኮምዩኒቲ ሺልድ አሸናፊ ማድረግ ቻለ፡፡
    ዝላታን ኢብራሂሞቪችን የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ሁሌም እንዲያስታውሱት የሚያደርጉ 5 ነገሮች በአንድ የውድድር ዘመን 28 ጎሎችን በሁሉም ውድድሮች በማስቆጠር በርካቶችን ያስገረመው ዝላታን ኢብራሂሞቪች የደረሰበት ከባድ የጉልበት ጉዳት በቀጣይ አመት በቲያትር ኦፍ ድሪምስ የዩናይትድ ደጋፊያን እንዳይመለከቱት አድርጓል፡፡ ተከታዩ ጽሁፍም ስዊዲናዊው አጥቂ ባሳለፍነው አመት በዩናይትድ ቤት ያደረጋቸውን እና በደጋፊዎች ዘንድም እንዳይረሳ የሚያደርጉትን 5 ጉዳዩች ያስመለክተናል፡፡ አለም ሆይ ቀጣይ ክለቤ ማንችስተር ዩናይትድ እንደሆነ እወቅልኝ ሲል የዩናይትድ ተጫዋች መሆኑን በይፋ ለአለም ባሳወቀ በአመቱ ቀያይ ሰይጣኖቹ እና ስዊዲናዊው ተለያይተዋል፡፡ የመጀመሪያውን የክለቡን ጨዋታውን ባደረገበት የስዊዲኑ ስቶኮልምም የኢሮፓ ሊግ ዋንጫን ከፍ በማድረግ በድል ቀያይ ሰይጣኖቹን ተሰናብቷል፡፡ እድሜው ከ30 በላይ ከሆነ በኋላ እያደር እንደ ወይን የጣፈጠው ስዊዲናዊው አጥቂ ከ250 በላይ ግቦችን ባለፉት 5 አመታት ከመረብ ማገናኘት ችሏል፡፡ በኮምዩኒቲ ሺልድ ሌሲስተር ሲቲ ላይ ያስቆጠራት ወሳኝ ግብ በርካቶች ሊጉን ሲቀላቀል በዚህ እድሜው ቢሉም ስዊዲናዊው ግን በርካቶችን ዝም ማሰኘት የቻለው ገና ከወዲሁ ነበር፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ የኤፍ ኤካፕ አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ በእንግሊዝ ኮምዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ከሊጉ አሸናፊ ሌስተር ሲቲ ጋር ባደረገው ጨዋታ ዩናይትድን ባለድል ያደረገች ወሳኝ ግብ ጨዋታው መገበዳጃ ሰአት ላይ በጭንቅላቱ ገጭቶ ማስቆጠሩን ተከትሎ ቀያይ ሰይጣኖቹን ከአመታት በኋላ የኮምዩኒቲ ሺልድ አሸናፊ ማድረግ ቻለ፡፡
    ETHIOADDISSPORT.COM
    ዝላታን ኢብራሂሞቪችን የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ሁሌም እንዲያስታውሱት የሚያደርጉ 5 ነገሮች
    በአንድ የውድድር ዘመን 28 ጎሎችን በሁሉም ውድድሮች በማስቆጠር በርካቶችን ያስገረመው ዝላታን ኢብራሂሞቪች የደረሰበት ከባድ የጉልበት ጉዳት በቀጣይ አመት በቲያትር ኦፍ ድሪምስ የዩናይትድ ደጋፊያን እንዳይመለከቱት አድርጓል፡፡ ተከታዩ ጽሁፍም ስዊዲናዊው አጥቂ ባሳለፍነው አመት በዩናይትድ ቤት ያደረጋቸውን እና በ…
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • አሳፋሪ : የዋሊያዎቹ ስብስብ በጥቋቁሮቹ ኮከቦች በሰፊ የጎል ልዩነት ተረምርሞ የምድቡን ግርጌ ታኮ ተቀመጠ

    በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ለማድረግ ወደጋና ኩማሲ ያቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከትልቅ የጨዋታ ብልጫ ጋር በጥቋቁሮቹ ኮከቦች በ 5-0 ሰፊ ውጤት ተረቶ የምድቡን ግርጌ ታኮ ለመቀመጥ ተገደደ።

    ከጨዋታው መጀመር በፊት በሰፊ ጎል የማሸነፍ የቅድሚያ ተገማችነት ያገኙት ጋናዎች ከጨዋታው መጀመር ጀምሮ ኳስን ይዞ በመጫወትና ወደፊት በመሄድ የተቃራኒያቸውን ተከላካይ መስመር ሰብሮ በመግባት ተከላክሎ ለመጫወት ሙከራ ያደረገውን የዋሊያዎችን ስብስብ ከጥቅም ውጪ በማድረግ ወሳኝ ሶስት ነጥብ በሜዳቸው አግኝተዋል።

    ጥቋቁሮቹ ኮከቦች ከእረፍት በፊት ሶስት ጎል ባስቆጠሩበት ጨዋታ ላይ ያስመዘገቡት ውጤት ኬንያን በማሸነፍ በምድቡ ሶስት ነጥብ ይዛ ከምትገኘው ሴራሊዮን በጎል ልዩነት በልጠው ምድቡን በአንደኝነት እንዲመሩ አስችሏቸዋል።

    የጨዋታውን ትንተና፣ የሜዳና ከሜዳ ውጪ ሁነት እንዲሁም የየቡድኖችን አባላት አስተያየቶችና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች በቀጣይ ይዘን የምንቀርብ ይሆናል።
    አሳፋሪ : የዋሊያዎቹ ስብስብ በጥቋቁሮቹ ኮከቦች በሰፊ የጎል ልዩነት ተረምርሞ የምድቡን ግርጌ ታኮ ተቀመጠ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ለማድረግ ወደጋና ኩማሲ ያቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከትልቅ የጨዋታ ብልጫ ጋር በጥቋቁሮቹ ኮከቦች በ 5-0 ሰፊ ውጤት ተረቶ የምድቡን ግርጌ ታኮ ለመቀመጥ ተገደደ። ከጨዋታው መጀመር በፊት በሰፊ ጎል የማሸነፍ የቅድሚያ ተገማችነት ያገኙት ጋናዎች ከጨዋታው መጀመር ጀምሮ ኳስን ይዞ በመጫወትና ወደፊት በመሄድ የተቃራኒያቸውን ተከላካይ መስመር ሰብሮ በመግባት ተከላክሎ ለመጫወት ሙከራ ያደረገውን የዋሊያዎችን ስብስብ ከጥቅም ውጪ በማድረግ ወሳኝ ሶስት ነጥብ በሜዳቸው አግኝተዋል። ጥቋቁሮቹ ኮከቦች ከእረፍት በፊት ሶስት ጎል ባስቆጠሩበት ጨዋታ ላይ ያስመዘገቡት ውጤት ኬንያን በማሸነፍ በምድቡ ሶስት ነጥብ ይዛ ከምትገኘው ሴራሊዮን በጎል ልዩነት በልጠው ምድቡን በአንደኝነት እንዲመሩ አስችሏቸዋል። የጨዋታውን ትንተና፣ የሜዳና ከሜዳ ውጪ ሁነት እንዲሁም የየቡድኖችን አባላት አስተያየቶችና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች በቀጣይ ይዘን የምንቀርብ ይሆናል።
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • “ማንችስተር ዩናይትድ ከ አልቫሮ ሞራታ ይልቅ ሀሪኬንን ማስፈረም አለበት” ፖል ሜርሰን

    አልቫሮ ሞራታ ከዩናይትድ ይልቅ ለለንደኑ ክለብ መፈረም እንዳለበት የስካይ ስፖርቱ ተንታኝ ገልፅዋል፡፡


    ቀያዮቹ ሰይጣኖች ለስፔናዊው አጥቂ 52 ሚሊየን ፓውንድ ለሪያልማድሪድ በዚህ ሳምንት ቢያቀርቡም የቻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው ክለብ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል፡፡ ሎስ ብላንዎቹ ከ70 ሚሊየን ፓውንድ በላይ ካልሆነ ለተጫዋቹ የሚመጡ ማንኛውንም የእንግዛቹ ጥያቄዎች እንደማያስተናግዱም ማሳወቃቸው በስፋት ተነግሯል፡፡

    Should Man Utd break the bank for Harry Kane?

    የስካይ ስፖርቱ ተንታኝ ፖል ሜርሰን በሰሞንኛው የአልቫሮ ሞራታ ስሙ በዝውውር ከ ማንችሰተር ዩናይትዶች ጋር መያያዙን ተከትሎ “ማንችስተር ዩናይትድ ከ አልቫሮ ሞራታ ይልቅ ሀሪኬንን ማስፈረም አለበት ” ሲል ተናግሯል፡፡ እንደ አምናው ሪከርድ ሰብረው የአለማችንን ውድ ተጫዋቾች የሚያስፈርሙ ከሆነ እንግሊዛዊው አጥቂ ሀሪኬን ምርጫቸው ሊሆን አንደሚገባ ለስካይ ስፖርት ያብራራው ተንታኙ እንደ ምክንያትነትም ሲያስቀምጥ በጠንካራው ሊግ ላይ 25 ግቦችን በአመት ውስጥ ማስቆጠር ለሚችል አጥቂ ከ90 እስከ 100 ሚሊየን ፓውንድ ማውጣት ያን ያህል የክለቡን በፋይናንስ እንደማይጎዳ ገልጽዋል፡፡

    Alvaro Morata: Would he suit Chelsea better than Man Utd?

    ማንችስተር ዩናይትድ በአለም ላይ ካሉ ትልቅ ክለቦች ውስጥ አንዱ ነው ይህ ክለብ በሚቀጥሉት ቅርብ አመታት የሊጉን ዋንጫ ማንሳት አለበት እንደ ከዚህ ቀደሙ 4ውስጥ ለመጨረስ መስራት የለበትም በማለት ሀሳቡን የቀጠለው ስመ ጥሩው ተንታኝ ሀሪ ኬን ግዢ ባይሳካም ስሙ በስፋት ከቼልሲ ጋር እየተነሳ የሚገኘው ሮሜሎ ሉካኮም ሌላኛው ምርጫቸው እንደሆነ ጨምሮ ገልፅዋል፡፡ ለካኮ ከቼልሲ ይልቅ ለማንችሰተር ዩናይትድ አጨዋወት የሚሆን አይነት ተጫዋች ነው ቼልሲ አልቫሮ ሞራታን የግሉ ቢያደርግ ተጠቃሚ ይሆናል ሲል ሀሳቡን አገባዷል፡፡
    “ማንችስተር ዩናይትድ ከ አልቫሮ ሞራታ ይልቅ ሀሪኬንን ማስፈረም አለበት” ፖል ሜርሰን አልቫሮ ሞራታ ከዩናይትድ ይልቅ ለለንደኑ ክለብ መፈረም እንዳለበት የስካይ ስፖርቱ ተንታኝ ገልፅዋል፡፡ ቀያዮቹ ሰይጣኖች ለስፔናዊው አጥቂ 52 ሚሊየን ፓውንድ ለሪያልማድሪድ በዚህ ሳምንት ቢያቀርቡም የቻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው ክለብ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል፡፡ ሎስ ብላንዎቹ ከ70 ሚሊየን ፓውንድ በላይ ካልሆነ ለተጫዋቹ የሚመጡ ማንኛውንም የእንግዛቹ ጥያቄዎች እንደማያስተናግዱም ማሳወቃቸው በስፋት ተነግሯል፡፡ Should Man Utd break the bank for Harry Kane? የስካይ ስፖርቱ ተንታኝ ፖል ሜርሰን በሰሞንኛው የአልቫሮ ሞራታ ስሙ በዝውውር ከ ማንችሰተር ዩናይትዶች ጋር መያያዙን ተከትሎ “ማንችስተር ዩናይትድ ከ አልቫሮ ሞራታ ይልቅ ሀሪኬንን ማስፈረም አለበት ” ሲል ተናግሯል፡፡ እንደ አምናው ሪከርድ ሰብረው የአለማችንን ውድ ተጫዋቾች የሚያስፈርሙ ከሆነ እንግሊዛዊው አጥቂ ሀሪኬን ምርጫቸው ሊሆን አንደሚገባ ለስካይ ስፖርት ያብራራው ተንታኙ እንደ ምክንያትነትም ሲያስቀምጥ በጠንካራው ሊግ ላይ 25 ግቦችን በአመት ውስጥ ማስቆጠር ለሚችል አጥቂ ከ90 እስከ 100 ሚሊየን ፓውንድ ማውጣት ያን ያህል የክለቡን በፋይናንስ እንደማይጎዳ ገልጽዋል፡፡ Alvaro Morata: Would he suit Chelsea better than Man Utd? ማንችስተር ዩናይትድ በአለም ላይ ካሉ ትልቅ ክለቦች ውስጥ አንዱ ነው ይህ ክለብ በሚቀጥሉት ቅርብ አመታት የሊጉን ዋንጫ ማንሳት አለበት እንደ ከዚህ ቀደሙ 4ውስጥ ለመጨረስ መስራት የለበትም በማለት ሀሳቡን የቀጠለው ስመ ጥሩው ተንታኝ ሀሪ ኬን ግዢ ባይሳካም ስሙ በስፋት ከቼልሲ ጋር እየተነሳ የሚገኘው ሮሜሎ ሉካኮም ሌላኛው ምርጫቸው እንደሆነ ጨምሮ ገልፅዋል፡፡ ለካኮ ከቼልሲ ይልቅ ለማንችሰተር ዩናይትድ አጨዋወት የሚሆን አይነት ተጫዋች ነው ቼልሲ አልቫሮ ሞራታን የግሉ ቢያደርግ ተጠቃሚ ይሆናል ሲል ሀሳቡን አገባዷል፡፡
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • “ተዉ አታበላሹ እንጂ…”

    ኤፍሬም እንዳለ

    እንዴት ሰነበታችሁሳ!
    በዛ ሰሞን ነው…በተቆፈረው የከተማው አንድ ክፍል፡፡ በአሥራዎቹ መጀመሪያ የሚሆኑ ልጆች የተቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ከርቀት ድንጋይ እየወረወሩ ይፎካከራሉ፡፡ ይሄኔ አንድ አዛውንት ምን ቢሉ ጥሩ ነው…
    “ልጆች ተዉ አታበላሹ እንጂ፣ ለእናንተ ነው እኮ የተቆፈረው፡፡”
    እንግዲህ ምን ያስቡ፣ ምን እግዚአብሔር ይወቀው፡፡ ግን ነገርዬዋ…አለ አይደል…ለሌላውም ታገለግላለች፡፡
    “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡
    ስሙኝማ…ሰኔ ገባ አይደል፣ በጀት መዝጊያ ጊዜ!… እኔ የምለው… ያለአግባብ ምን ሆነ የተባለ ስንት ቢሊዮን ብር ነው! እንዴት ነው…ነገርዬው ሁሉ ሀዲዱን የሳተ ባቡር እየሆነ ያለው! በሚሊዮኖች ስንገረም፣ በመቶ ሚሊዮኖች ስንገረም፣ ጭራሽ ቢሊዮኖች ገባና አረፈው!
    እናማ…“ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡
    ዘንድሮ…አለ አይደል…ሁሉም ነገሮችን የሚያየው ከራሱ ሆኗል፡፡ እሱ ከደላው ሁሉም ሰው የደላው ይመስለዋል፣ እሱ አሼሼ ገዳሜ ካለ ሁሉም ሰው አሼሼ ገዳሜ የሚል ይመስለዋል፡፡ በሆነ ነገር ‘ሙያተኛ’ የሆኑት ሰዎች ሙያው የሚጠይቀውን ማብራሪያ ከመስጠት እንደራሳቸው ጓዳ ብቻ ሲያስቡት አስቸጋሪ ነው፡፡
    “ቲማቲም እንዲህ የተወደደችበትን ምክንያት ልታስረዳኝ ትችላለህ?…”
    “መሠረታዊ የሆነ ጥያቄ ነው ያመጣኸው፡፡ ይገርምሀል፣ ይሄን ጥያቄ መቼ ነው የምጠየቀው ብዬ አስብ ነበር፡፡ ዋናው ነገር በመጀመሪያ ቲማቲም ምን አይነት ጥቅም እንደሚሰጥ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡”
    ሰውየው ምን ነካው! የቲማቲም እርሻ አለው እንዴ!
    ስለ ዋጋው መወደድ ጠየቅሁት እንጂ የካሎሪና የቪታሚን ዝርዝር አቅርብልኝ አልኩት!
    “ይቅርታ፣ መቼም ስለ ቲማቲም ጥቅም የማያውቅ አለ ለማለት ያስቸግራል፡፡ አሁን ማወቅ የምፈልገው ዋጋው እንደ ጠፈር መንኮራኩር ሽቅብ ለምን እንደተተኮሰ ነው፡፡
    “እኮ መወደዱ ከሚሰጠው ጥቅም ጋር መያዝ አለበት፡፡ ቲማቲም ተወደደ ማለት ብቻ ሳይሆን ዋናው ማወቅ የሚገባን ከሚሰጠው ጥቅም አንጻር ለምን ኪሎ መቶ ብር አይገባም…”
    ይቺን ይወዳል! “ኧረ አንተኑ መቶ…” ብላችሁ ትጀምሩና ትተዉታላችሁ፡፡ ልክ እኮ ቲማቲም አዲስ የተገኘች ግኝት ሆና ገና “ጉድ! ጉድ!” እየተባለላት ያለች ነገር ያስመስላታል፡፡
    “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡
    እናላችሁ… ስንት ዘመን ስንጠቀምባቸው የኖርናቸው ነገሮች…አለ አይደል… በፈረንጂኛ ስለተጻፈላቸው ብቻ የሆነ አዲስ ግኝት የተገኘ ይመስል ስናደርገው የሆነ ችግር አለ፡፡
    “ስለ ጤፍስ ምን ታስባለህ?”
    “ጤፍማ አሁን ዓለም አቀፋዊ ሆናለች፣ በእውነት ደስ የሚል ነው፡፡”
    “ደስ የሚል ነው የሚለውን ብታስረዳኝ…”
    “ፈረንጆች ጤፍን መውደዳቸው በጣም ደስ ይላል፣ ይህ ጤፍ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እያገኘ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡”
    “ፈረንጅ ወደደው አልወደደው የጤፍን ደረጃ የሚቀንሰው ነገር አለ እንዴ! ለምንድነው ስንት ሺህ ዓመት ስንጠቀምበት ኖረን አሁን የምንዘምርለትን ያህል ሳንዘምርለት የኖርነው!”
    “አልገባህም፣ ዋናው ነገር ጤፍ ዓለም አቀፍ መሆኗ ለመልካም ገጽታ ግንባታ ያግዛል፡፡ ‘ጤፍ’ የሚለው ነገር ሲነሳ የኢትዮዽያም ስም አብሮ ይነሳል…”
    ቆይማ…የኢትዮዽያ ስም እንዲነሳ የሚያደርጉ መአት ነገሮች አሉ እኮ! ስንት በአንድ ወይ በሌላ ምክንያት ላያቸው ላይ የተቀመጥንባቸው… አለ አይደል… የፈረደበት ፈረንጅ ‘እስኪያወራላቸው’ የምንጠብቃቸው ስንት ነገሮች አሉ እኮ!
    እኔ የምለው…እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ… ይቺ ‘የመልካም ገጽታ ግንባታ’ የሚሏት ነገር እንዴት ነው እንዲህ መጫወቻ የሆነችው! አሸር በአሸር የሆነውን ‘ዲስኩር’ ሁሉ ማሳመሪያ ሆና ‘ኩል፣’ ‘ፋውንዴሽን’ ምናምን አስመሰልናት እኮ!
    “ድርጅታችን የአገሪቱን መልካም ገጽታ በውጪ ለመገንባት አቅዶ እየሠራ ነው…” አይነት ‘ወሬ’ ማሳመሪያ ተለምዷል፡፡ ድርጀቱ እኮ እንኳን የአገር ገዕታ ሊገነባ ራሱ ገጽታ የሚባል ነገር የለውም! ቂ…ቂ…ቂ… ግን በዚህ የአገር ገጽታ ለመገንባት መካከለኛ ገቢ ለመድረስ ምናምን የሚባሉ ‘ዲስኩር’ ማሳመሪያዎች ላይ “እንዴት?” “ለምን?” አይነት ጥያቄዎች ስለማይነሱ እንደተፈለገው መደጋገም ይቻላል፡፡ እናማ… ይቺ ‘መልካም ገፅታ ግንባታ’ የምትለዋ ሀረግ… ጠቃሚነቷ ሳስቶ ትርጉም አልባ እንዳትሆንማ!”
    “እኔ እንዲህ የሚሉ ብዙ ሰዎች ከልባቸው ሳይሆን ‘እነ እከሌ ብለውት እኔ ሳልለው እንዳልቀር’ ብለው ይመስለኛል፡፡ ጤፍን ከአገር መልካም ገፅታ ጋር ማያያዝ…”
    “ቆይ! ቆይ! እንዲህ ስትል ምን ማለትህ ነው? አንተ እንደ ጠላቶቻችን የዚችን አገር እድገት አትፈልግም እንዴ? አንተ…”
    አሁን ነገር መጣ! አሁን ገና ዋናው ነገር መጣ! አሁን ገና የአገር በሽታ እየሆነ ያለ ነገር መጣ! በሆነ አቋም ላይ ጠንከር ብላችሁ ከተከራከራችሁ…እንዲህ አይነት ነገር እንደሚመጣ ጠብቁ፡፡ ሀሳቦቻችሁን የምታራምዱ ሳይሆን ከጀርባ ሌላ ዓላማ ያላችሁ አስመስለው ‘ጎመን በጤና’ እንድትሉ ያደርጓችኋል፡፡
    “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡
    “እሺ በአጠቃላይ የዋጋ መወደድ ምክንያት ምንድነው ትላለህ?”
    “እሱ እንኳን የእድገት ምልክት ነው፡፡”
    “ይቅርታ የብዙ ነገሮች ዋጋ ተወደደ፣ ከአቅማችን በላይ ሆነ፣ ኑሮ ከፋ እያልኩህ እኮ ነው!”
    “እኮ እኔስ ምንድነው የምልህ…ይሀ ሁሉ ምን ያህል እያደግን እንደሆንን የሚያሳይ ነው፡፡”
    “በነገራችን ላይ እየሠራኸው የነበረው ቤት ምን ደረሰ?”
    “እሱማ አለቀና አከራየሁት እኮ፡፡ እንደውም ሲ.ኤም.ሲ. የተጀመረ ጂ ፕላስ ቱ ገዝቼ እየሠራሁ ነው፡፡”
    “ታዲያ መጀመሪያውኑ እንዲህ አትለኝም!” ትላላችሁ በሆዳችሁ፡፡ ግን ደግሞ ዝም ብሎ ማለፉም አላስችል ይላል፡፡
    “ለምሳሌ እኛ ቤት ቁርስ መብላት ትተናል። የምሳ ፍጆታችንም በአርባ ስምንት በመቶ አቆልቁሏል። ይቅርታ እዚህ አገር ሁሉንም ነገር በመቶኛ ማስላት የማይሸረፍ ሰብዊ መብት ስለሆነ ነው ቁጥር የጠቀስኩት፡፡”
    “ምን እያልክ ነው…”
    “እኔም፣ የማውቃቸውም ሰዎች የምንበላው እየቸገረን እንዴት የእድገት ምልክት ነው ትለኛለህ!”
    “እሱ የአንተ ጉዳይ ነው፡፡”
    “ለምሳሌ ድሮ ለምሳዬ ሁለት አይነት ምግብ እበላ ነበር፡ ዘንድሮ ግን አልሆነም፡፡”
    “እሱ እንግዲህ…”
    “ለምሳሌ በፊት ግፋ ቢል ፓራሳይቷ ምናምን ብታስቸግረኝ ነው…አሁን ግን የበሽታ አይነት በሙሉ ሰፍሮብናል፣ ይሄም የእድገት ምልክት ነው?…”
    እግረ መንገዴን ይቺን ስሙኝማ…ሰዓሊው ሴትዮዋን እየሳላት ነበር፡፡ ሲጨርስም አቀረበላትና…
    “ምን ይመስልሻል…” ይላታል፡፡
    እሷም ግንባሯን ቋጥራ “ምን በደልኩህ! ምን ብበድልህ ነው እንዲህ አድርገህ የምትስለኝ…” ትለዋለች፡፡
    ሰዓሊው ይደነግጥና “ምነው፣ ምን አጠፋሁ!” ይላታል፡፡ እሷ እየተንገሸገሸች…
    “ጦጣ ነው እኮ ያስመሰልከኝ!…” ትላለች፡፡
    ይሄኔ ሰዓሊው ሳቅ ብሎ ምን ቢላት ጥሩ ነው… “እሱ የእኔ ሳይሆን የወላጆችሽ ጥፋት ነው…” ብሏት አረፈው፡፡
    ሰው ከመውቀስ በፊት ጥፋቱ የማን እንደሆነ ይለይማ!
    እናማ…“ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡
    ደህና ሰንብቱልኝማ!
    “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ኤፍሬም እንዳለ እንዴት ሰነበታችሁሳ! በዛ ሰሞን ነው…በተቆፈረው የከተማው አንድ ክፍል፡፡ በአሥራዎቹ መጀመሪያ የሚሆኑ ልጆች የተቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ከርቀት ድንጋይ እየወረወሩ ይፎካከራሉ፡፡ ይሄኔ አንድ አዛውንት ምን ቢሉ ጥሩ ነው… “ልጆች ተዉ አታበላሹ እንጂ፣ ለእናንተ ነው እኮ የተቆፈረው፡፡” እንግዲህ ምን ያስቡ፣ ምን እግዚአብሔር ይወቀው፡፡ ግን ነገርዬዋ…አለ አይደል…ለሌላውም ታገለግላለች፡፡ “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡ ስሙኝማ…ሰኔ ገባ አይደል፣ በጀት መዝጊያ ጊዜ!… እኔ የምለው… ያለአግባብ ምን ሆነ የተባለ ስንት ቢሊዮን ብር ነው! እንዴት ነው…ነገርዬው ሁሉ ሀዲዱን የሳተ ባቡር እየሆነ ያለው! በሚሊዮኖች ስንገረም፣ በመቶ ሚሊዮኖች ስንገረም፣ ጭራሽ ቢሊዮኖች ገባና አረፈው! እናማ…“ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡ ዘንድሮ…አለ አይደል…ሁሉም ነገሮችን የሚያየው ከራሱ ሆኗል፡፡ እሱ ከደላው ሁሉም ሰው የደላው ይመስለዋል፣ እሱ አሼሼ ገዳሜ ካለ ሁሉም ሰው አሼሼ ገዳሜ የሚል ይመስለዋል፡፡ በሆነ ነገር ‘ሙያተኛ’ የሆኑት ሰዎች ሙያው የሚጠይቀውን ማብራሪያ ከመስጠት እንደራሳቸው ጓዳ ብቻ ሲያስቡት አስቸጋሪ ነው፡፡ “ቲማቲም እንዲህ የተወደደችበትን ምክንያት ልታስረዳኝ ትችላለህ?…” “መሠረታዊ የሆነ ጥያቄ ነው ያመጣኸው፡፡ ይገርምሀል፣ ይሄን ጥያቄ መቼ ነው የምጠየቀው ብዬ አስብ ነበር፡፡ ዋናው ነገር በመጀመሪያ ቲማቲም ምን አይነት ጥቅም እንደሚሰጥ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡” ሰውየው ምን ነካው! የቲማቲም እርሻ አለው እንዴ! ስለ ዋጋው መወደድ ጠየቅሁት እንጂ የካሎሪና የቪታሚን ዝርዝር አቅርብልኝ አልኩት! “ይቅርታ፣ መቼም ስለ ቲማቲም ጥቅም የማያውቅ አለ ለማለት ያስቸግራል፡፡ አሁን ማወቅ የምፈልገው ዋጋው እንደ ጠፈር መንኮራኩር ሽቅብ ለምን እንደተተኮሰ ነው፡፡ “እኮ መወደዱ ከሚሰጠው ጥቅም ጋር መያዝ አለበት፡፡ ቲማቲም ተወደደ ማለት ብቻ ሳይሆን ዋናው ማወቅ የሚገባን ከሚሰጠው ጥቅም አንጻር ለምን ኪሎ መቶ ብር አይገባም…” ይቺን ይወዳል! “ኧረ አንተኑ መቶ…” ብላችሁ ትጀምሩና ትተዉታላችሁ፡፡ ልክ እኮ ቲማቲም አዲስ የተገኘች ግኝት ሆና ገና “ጉድ! ጉድ!” እየተባለላት ያለች ነገር ያስመስላታል፡፡ “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡ እናላችሁ… ስንት ዘመን ስንጠቀምባቸው የኖርናቸው ነገሮች…አለ አይደል… በፈረንጂኛ ስለተጻፈላቸው ብቻ የሆነ አዲስ ግኝት የተገኘ ይመስል ስናደርገው የሆነ ችግር አለ፡፡ “ስለ ጤፍስ ምን ታስባለህ?” “ጤፍማ አሁን ዓለም አቀፋዊ ሆናለች፣ በእውነት ደስ የሚል ነው፡፡” “ደስ የሚል ነው የሚለውን ብታስረዳኝ…” “ፈረንጆች ጤፍን መውደዳቸው በጣም ደስ ይላል፣ ይህ ጤፍ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እያገኘ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡” “ፈረንጅ ወደደው አልወደደው የጤፍን ደረጃ የሚቀንሰው ነገር አለ እንዴ! ለምንድነው ስንት ሺህ ዓመት ስንጠቀምበት ኖረን አሁን የምንዘምርለትን ያህል ሳንዘምርለት የኖርነው!” “አልገባህም፣ ዋናው ነገር ጤፍ ዓለም አቀፍ መሆኗ ለመልካም ገጽታ ግንባታ ያግዛል፡፡ ‘ጤፍ’ የሚለው ነገር ሲነሳ የኢትዮዽያም ስም አብሮ ይነሳል…” ቆይማ…የኢትዮዽያ ስም እንዲነሳ የሚያደርጉ መአት ነገሮች አሉ እኮ! ስንት በአንድ ወይ በሌላ ምክንያት ላያቸው ላይ የተቀመጥንባቸው… አለ አይደል… የፈረደበት ፈረንጅ ‘እስኪያወራላቸው’ የምንጠብቃቸው ስንት ነገሮች አሉ እኮ! እኔ የምለው…እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ… ይቺ ‘የመልካም ገጽታ ግንባታ’ የሚሏት ነገር እንዴት ነው እንዲህ መጫወቻ የሆነችው! አሸር በአሸር የሆነውን ‘ዲስኩር’ ሁሉ ማሳመሪያ ሆና ‘ኩል፣’ ‘ፋውንዴሽን’ ምናምን አስመሰልናት እኮ! “ድርጅታችን የአገሪቱን መልካም ገጽታ በውጪ ለመገንባት አቅዶ እየሠራ ነው…” አይነት ‘ወሬ’ ማሳመሪያ ተለምዷል፡፡ ድርጀቱ እኮ እንኳን የአገር ገዕታ ሊገነባ ራሱ ገጽታ የሚባል ነገር የለውም! ቂ…ቂ…ቂ… ግን በዚህ የአገር ገጽታ ለመገንባት መካከለኛ ገቢ ለመድረስ ምናምን የሚባሉ ‘ዲስኩር’ ማሳመሪያዎች ላይ “እንዴት?” “ለምን?” አይነት ጥያቄዎች ስለማይነሱ እንደተፈለገው መደጋገም ይቻላል፡፡ እናማ… ይቺ ‘መልካም ገፅታ ግንባታ’ የምትለዋ ሀረግ… ጠቃሚነቷ ሳስቶ ትርጉም አልባ እንዳትሆንማ!” “እኔ እንዲህ የሚሉ ብዙ ሰዎች ከልባቸው ሳይሆን ‘እነ እከሌ ብለውት እኔ ሳልለው እንዳልቀር’ ብለው ይመስለኛል፡፡ ጤፍን ከአገር መልካም ገፅታ ጋር ማያያዝ…” “ቆይ! ቆይ! እንዲህ ስትል ምን ማለትህ ነው? አንተ እንደ ጠላቶቻችን የዚችን አገር እድገት አትፈልግም እንዴ? አንተ…” አሁን ነገር መጣ! አሁን ገና ዋናው ነገር መጣ! አሁን ገና የአገር በሽታ እየሆነ ያለ ነገር መጣ! በሆነ አቋም ላይ ጠንከር ብላችሁ ከተከራከራችሁ…እንዲህ አይነት ነገር እንደሚመጣ ጠብቁ፡፡ ሀሳቦቻችሁን የምታራምዱ ሳይሆን ከጀርባ ሌላ ዓላማ ያላችሁ አስመስለው ‘ጎመን በጤና’ እንድትሉ ያደርጓችኋል፡፡ “ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡ “እሺ በአጠቃላይ የዋጋ መወደድ ምክንያት ምንድነው ትላለህ?” “እሱ እንኳን የእድገት ምልክት ነው፡፡” “ይቅርታ የብዙ ነገሮች ዋጋ ተወደደ፣ ከአቅማችን በላይ ሆነ፣ ኑሮ ከፋ እያልኩህ እኮ ነው!” “እኮ እኔስ ምንድነው የምልህ…ይሀ ሁሉ ምን ያህል እያደግን እንደሆንን የሚያሳይ ነው፡፡” “በነገራችን ላይ እየሠራኸው የነበረው ቤት ምን ደረሰ?” “እሱማ አለቀና አከራየሁት እኮ፡፡ እንደውም ሲ.ኤም.ሲ. የተጀመረ ጂ ፕላስ ቱ ገዝቼ እየሠራሁ ነው፡፡” “ታዲያ መጀመሪያውኑ እንዲህ አትለኝም!” ትላላችሁ በሆዳችሁ፡፡ ግን ደግሞ ዝም ብሎ ማለፉም አላስችል ይላል፡፡ “ለምሳሌ እኛ ቤት ቁርስ መብላት ትተናል። የምሳ ፍጆታችንም በአርባ ስምንት በመቶ አቆልቁሏል። ይቅርታ እዚህ አገር ሁሉንም ነገር በመቶኛ ማስላት የማይሸረፍ ሰብዊ መብት ስለሆነ ነው ቁጥር የጠቀስኩት፡፡” “ምን እያልክ ነው…” “እኔም፣ የማውቃቸውም ሰዎች የምንበላው እየቸገረን እንዴት የእድገት ምልክት ነው ትለኛለህ!” “እሱ የአንተ ጉዳይ ነው፡፡” “ለምሳሌ ድሮ ለምሳዬ ሁለት አይነት ምግብ እበላ ነበር፡ ዘንድሮ ግን አልሆነም፡፡” “እሱ እንግዲህ…” “ለምሳሌ በፊት ግፋ ቢል ፓራሳይቷ ምናምን ብታስቸግረኝ ነው…አሁን ግን የበሽታ አይነት በሙሉ ሰፍሮብናል፣ ይሄም የእድገት ምልክት ነው?…” እግረ መንገዴን ይቺን ስሙኝማ…ሰዓሊው ሴትዮዋን እየሳላት ነበር፡፡ ሲጨርስም አቀረበላትና… “ምን ይመስልሻል…” ይላታል፡፡ እሷም ግንባሯን ቋጥራ “ምን በደልኩህ! ምን ብበድልህ ነው እንዲህ አድርገህ የምትስለኝ…” ትለዋለች፡፡ ሰዓሊው ይደነግጥና “ምነው፣ ምን አጠፋሁ!” ይላታል፡፡ እሷ እየተንገሸገሸች… “ጦጣ ነው እኮ ያስመሰልከኝ!…” ትላለች፡፡ ይሄኔ ሰዓሊው ሳቅ ብሎ ምን ቢላት ጥሩ ነው… “እሱ የእኔ ሳይሆን የወላጆችሽ ጥፋት ነው…” ብሏት አረፈው፡፡ ሰው ከመውቀስ በፊት ጥፋቱ የማን እንደሆነ ይለይማ! እናማ…“ተዉ አታበላሹ እንጂ…” ሊባልላቸው የሚገባ መአት ነገሮች አሉ፡፡ ደህና ሰንብቱልኝማ!
    0 Comments 0 Shares