የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ ወሰደ

0
0
የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።

በዚህ መሰረት የድርጅቱ ሊቀ መንበር አቶ አባይ ወልዱ ከድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው ተነስተው በድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲያገለግሉ ወስኗል።

በተጨማሪም የድርጅቱ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ በየነ ምክሩም ወደ ድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲሰሩ መወሰኑን ድርጅቱ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ከዚህ ባለፈም የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወይዘሮ አዜብ መስፍንን ከስራ አስፈጻሚ አባልነታቸው እና ማዕከላዊ ኮሚቴው ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑንም ገልጿል።

ድርጅቱ ከዚህ በተጨማሪም ለሌሎች ሁለት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

እርምጃው ማዕከላዊ ኮሚቴው ያካሄደውን ጥልቅ ግምገማ ተከትሎ የተወሰደ ነው።

ማዕከላዊ ኮሚቴው ባለፈው ሳምነት ባወጣው መግለጫ በአመራር ስትራቴጂካዊ ፖለቲካዊ ሁነቶች፣ ሁለንተናዊ የልማታዊ ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥ እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ በጥልቅ በመገምገም ያሉትን መሰረታዊ ክፍተቶች በዝርዝር ማየቱን ገልፆ ነበር።

በትግልና በመርህ የተመሰረተ አንድነት አለመኖር፣ በመጠቃቃትና መከላከል ዝምድና ላይ መመስረት፣ የፀረ ዴሞክራሲ ጥልቅ አስተሳሰብና ተግባራት መኖራቸውን መገምገሙንም በመግለጫው ማስታወቁ ይታወሳል።

በተጨማሪም የወጣቱን ትውልድ እና የምሁሩን አቅም በመገንባት፣ በማሰለፍና ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ መሰረታዊ ጉድለቶች መኖራቸውን ገምግሞ ነበር።

በክልሉም ትራንስፎርሜሽን ከማረጋገጥ አኳያ መሰረታዊ ስትራቴጂካዊ የአመራር ችግር እንደነበረበት በመገምገም፥ ባለፉት አመታት በተደረገው እንቅስቃሴ በገጠርና ከተማ የተመዘገቡ የልማት ድሎች መኖራቸውን ያረጋገጠ ቢሆንም ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳካት አኳያ የህዝቡ ተጠቃሚነት ከፍላጎቱ ጋር ሲመዘን ግን መሰረታዊ ችግሮች እንደነበሩበት በመገምግም ማረጋገጡንም ነበር በመግለጫው የጠቀሰው።

ማእከላዊ ኮሚቴው በቀሪ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ላይ ጥልቅ ሂስና ግለ ሂስ የቀጠለ ሲሆን፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የአመራር መልሶ ማደራጀት እንደሚያደርግ አስታውቋል ።


በሙሉጌታ አፅብሃ
 
 
Search
Categories
Read More
Uncategorized
ዳይ እየተሰዳደብን ...
«ዘውድአለም ታደሰ» ሰው ሁሉ የፖለቲካ ተንታኝ ሆኖልኛል። ጭራሽ እየሩሳሌምን ለእስራኤል አሳልፈን አንሰጥም! አንሰጥም!...
By Zewdalem 2017-12-07 12:34:35 0 0
Uncategorized
ልክ የዛሬ 21 ዓመት ይህ ሆኗል
በደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው የኮሞሮስ ደሴት ተመራጭ የጎብኚዎች መዳረሻ ስፍራ ነች። በህንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ሲዝናኑ የነበሩ ጎብኚዎች እና...
By Dawitda 2017-11-23 06:15:19 1 0
Uncategorized
The story behind the arrest of Mohammed Ali Al-Amoudi explained (Gossip)
The first troubling signs that Mohammed Ali Al-Amoudi (Sheikh) may, after all, have faced trying...
By rahwa 2017-11-13 16:15:40 1 0
Uncategorized
~~~~~~ Alert! Alert! Alert! ጥንቃቄ!!! ~~~~~
በሳዑዲ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን~~~~~~~~//~~~~~~~~//~~~~~~~~~ከነገ ማለትም እ.ኤ.አ ከኖቬምበር 15 ማለዳ ጀምሮ ላልተወሰኑ...
By Dawitda 2017-11-15 06:51:19 0 0
Uncategorized
ኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በመበደል ከዓለም ቀዳሚ ሃገራት አንዷ ነች ተባለ
ኢትዮጵያ ከቻይና በመቀጠል ከሶሪያ እኩል የኢንተርኔት እና የሞባይል ተጠቃሚዎች ላይ ገደቦችን በመጣል በዓለም ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች ሲል ፍሪደም ሃውስ...
By Seller 2017-11-16 11:27:06 0 0