ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ስልጣን እንደማይለቁ ገለፁ

0
0

በራሳቸው ፍቃድ ከፕሬዚዳንትነታቸው እንዲወርዱ ጫና እየተደረገባቸው ያሉት የዚምባቡዌው ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ትናንት በሰጡት መግለጫ ስልጣን እንደማይለቁ ተናግረዋል።

በቀጥታ የተሌቪዥን ስርጭት በተላለፈው መግለጫቸው በቀጣይ ታህሳስ ወር በሚደረገው የዛኑ ፒ ኤፍ አጠቃላይ ስበሰባ ላይም ፓርቲያቸውን በመምራት እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ ግን በትናነትናው እለት ሮበርት ሙጋቤን ከፓርቲው ሊቀመንበርነት ማንሳቱ ይታወሳል።

ሮበርት ሙጋቤ በ24 ሰዓት ውስጥ ስልጣናቸውን እንዲያስረክቡ፤ ካልሆነ ግን ስልጣናቸው እንደሚነጠቅ ፓርቲው በትናንትናው እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

የዚምባቡዌ ጦር ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ በሀገሪቱ ስልጣን ላይ ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ የፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ሀይል መቀነሱ እየተነገረ ይገኛል።

ሮበት ሙጋቤ የሀገሪቱን ምክትል ፕሬዚዳንት ኤሚርሰን ማኛንጋዋን ከስልጣን ማንሳታቸውን ተከትሎ ነው ይህ ሁሉ ቀውስ የተከሰተባቸው።

ይህንን ተከትሎም በራሳቸው ፍቃድ ከፕሬዚዳንትነታቸው እንዲወርዱ ጫና እየተደረገባቸው ሲሆን፥ በርካታ የሀገሪቱ ዜጎችም ፕሬዚዳንቱ በትናንትናው መግለጫቸው ስልጣን መልቀቃቸውን ይፋ ያደርጋሉ በሚል በመጠባበቅ ላይ ነበሩ።

በአንጻሩ ግን ሮበርት ሙጋቤ በጦር ጀነራሎች ታጅበው በሰጡት መግለጫ፥ “ስልጣኔን አልለቅም፤ ከሳምንታት በኋላ የሚደረገ የዛኑ ፒ ኤፍ ፓርቲ ኮንግረስን እመራለው” ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዚዳንቱ ከፓርቲያቸው፣ ከሀገሪቱ ጦር እና ከሀገሪቱ ህዝብ እየቀረበ ያለውን ቅሬታ እንደሚቀበሉ እና ዚምባቡዌን ወደ ቀድሞ ሰማሏ እንደሚመልሱ ተናግረዋል።

ለ20 ደቂቃ በቆየው መግለጫቸው እየቀረበላቸው ስላለው የስልጣን መልቀቅ ጥያቄና ስለ ባለቤታቸው ግሬስ ሙጋቤ የተናገሩት ነገር የለም ነው የተባለው።

“ጦሩ የሀገሪቱን ስልጣን መቆጣጠሩ እና እኔን በቤት ውስጥ በማሰሩ የሰራው ስህተት የለም” ሲሉም ተደምጠዋል።

ይሁን እንጂ ፓርቲያቸው ዛኑ ፒ ኤፍ ፕሬዚዳንቱ አስከ ዛሬ 7 ሰዓት ድረስ ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው የማይለቁ ከሆነ ፕሬዚዳንትነቱን እንደሚነጥቃቸው አስታውቋል።

ዛኔ ፒ ኤፍ ፓርቲ በትናንትናው እለት ባደረገው ስብሰባ ሮበርት ሙጋቤን ከፓርቲው ሊቀ መንበርነት ማንሳቱን አስታውቋል።

ባለቤታቸው ቀዳማዊ እመቤት ግሬስ ሙጋቤም ከፓርቲ አባልነታቸው መባረራቸውንም ፓርቲብ በትናንትናው እለት አሳውቋል።

ፓርቲው በፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ከስልጣን የተባረሩት የቀድመሞውን ምክትል ፕሬዚዳንት ኤመርሰን መኛንጋዋን ሊቀ መንበር ማድረጉን እየተነገረ ነው።

Like
1
ፍለጋ
Categories
Read More
Uncategorized
Ethiopia Travel Guide for Curious Travelers
For those seeking something different, here’s my Ethiopia travel guide that will hopefully...
By binid 2017-11-26 06:56:18 0 0
Art
How to get escorts in Dubai 0528648070 Verified Bur Dubai Escorts
How to get escorts in Dubai 0528648070 Verified Bur Dubai Escorts She left. She said that Dad...
By heenaparker516 2025-06-06 15:34:33 0 0
Uncategorized
እንቆቅልሽ የሆነው የወተት ምርት
ኢትዮጵያ በቀንድ ከብቶች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚውን ሥፍራ፣ በዓለም ከ10 አገሮች መካከል አንዷ ብትሆንም ከወተት ሀብቷ ማግኘት የሚገባትን ያህል ጥቅም...
By Seller 2017-12-22 07:02:06 1 0
Uncategorized
ወርቃማው ደብዳቤ !
(አሌክስ አብርሃም) እንዴት ናት ኢትዮጲያ እንዴት ነው አፈሩ ጤናቸው እንዴት ነው ጠቅላይ ሚንስትሩ ?ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህናናቸው...
By binid 2017-11-24 20:05:00 0 0
Art
Transcendent +971509530047 Tiktoker call girls in abu dhabi, social media call girls abu dhabi
Transcendent +971509530047 Tiktoker call girls in abu dhabi, social media call girls abu dhabi...
By heenaparker516 2025-06-06 15:37:19 0 0