መልካም አጋጣሚ ቁንጮ ነው __

0
0

ወጣቱ የአንድን አርሶ አደር ቆንጆ ልጃገረግ ማግባት ፈልጓል፡፡ እናም ወደ አባቷ ቀርቦ ፍቃዳቸው ይሆን ዘንድ ጥያቄውን አቀረበ፡፡ አባት ልጁን ከእግር ጥፍሩ እስከ እራስ ፀጉሩ እየተመለከቱት አንድ ተግባር ሰጡት፡፡ “ናስኪ ልጄ! ሂድና እዛ እመስኩ መሐል ቁምና እነዚህን ሦስት ኮርማዎች ተራበተራ እለቃቸዋለሁ፡፡ ከሦስቱ ኮርማ ያንደኛውን ኮርማ ጅራት የያዝክ እንደሁ ልጄን እድርልሃለሁ፡፡ ታገባታለህ” አሉት፡፡ ወጣቱ በታዘዘው መሰረት ከግጦሹ ሜዳ ሁኖ መጠባበቅ ጀመረ፡፡ የኮርማዎቹ በረት እንደተከፈተ ትልቅ ኮርማ ከዚህ በፊት አይቶት የማያውቅ ሻኛ የተሸከመ ኮርማ ሲመጣ ተመለከተው፡፡ ወጣቱ “ይሄስ ይለፈኝ የቀጣዩን ኮርማ እይዘዋለሁ” ብሎ ወሰነና አስተላለፈው፡፡ ሁለተኛው ሲመጣ የሚያየውን ማመን አልቻለም፡፡ ከመጀመሪያው በላቀ ግዙፍ ሆነበት፡፡ “የሚቀጥለው ኮርማ (ሦስተኛው ማለቱ ነው፡፡) የፈለገውን ይሁን እሱን እይዘዋለሁ” በማለት ይሄኛውን ወደ ጥግ በመሸሽ አሳለፈው፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ የኮርማዎች በር ሲከፈት ወጣቱ ፈገግ አለ፡፡ ከበረቱ የወጣው ኮርማ ደከም ያለ ነበር፡፡ ወጣቱ የኮርማውን ጅራት ለመያዝ እንዲያመቸው አቋቋሙኝ አስተካክሎ ጠበቀው፡፡ ኮርማው እሱጋ ሲደርስ ዘሎ ወጣበት ነገር ግን የኮርማውን ጅራት መያዝ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ኮርማው ጅራተ ቆራጣ ስለነበር ሙሉ ጅራት አልነበረውምና፡፡

ሕይወት በመልካም አጋጣሚዎች (Opportunities) የተሞላች ናት፡፡ አንዳንዱን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም ቀላል ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ አስቸጋሪ ነው፡፡ ነገር ግን የተሻለ ይገኛል በማለት እጅ የገባን መልካም እድል ማሳለፍ የማይመጣን እንደመጠበቅ ይቆጠራል፡፡ ምክንያቱም ያመለጠ መልካም አጋጣሚ መልሶ እራሱ አይመጣም፡፡ ይህ ማለት ግን ሌላ መልካም አጋጣሚ የለም ማለት አይደለም፡፡ የከፋ ወይም የተሻለ ይኖራል፤ይመጣልም፡፡ እራሱ የበፊቱ ግን አይመጣም፡፡ አንዴ ካመለጠ መልሶ እንደማይገኝ ሲናገሩ መልካም አጋጣሚ ቁንጮ ነው ይሉታል፡፡ ቁንጮ ልጆች በአብዛኛው በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ፊት ለፊት ላይ ቁጢጥ አድርገው የሚተውት የፀጉር አቆራረጥ ነው፡፡ መልካም አጋጣሚም እንደመጣ ፊት ለፊት ካልይዙት ዘወር ካለ መላጣ ስለሆነ መያዝ አይቻልም ሲሉ ነው ቁንጮ ነው ያሉት፡፡ ስለሆነም ሁሌም ከፊትህ የመጣን መልካም አጋጣሚ ይዋል ይድር ሳትል ተጠቀምበት ነው መልዕክቱ፡፡

ምንጭ፡ NEVER MISS FIRST OPPORTUNITY!

(#ምስጋናው ግሸን ወልደ አገሬ)

17-09-2007 ዓ.ምhttps://www.facebook.com/groups/bookforall/?fref=nf

Like
1
ፍለጋ
Categories
Read More
Uncategorized
‹‹በህልም የተፈጠረ መወስለት ከሐጢያት ይቆጠር ይሆን?››
‹‹በህልም የተፈጠረ መወስለት ከሐጢያት ይቆጠር ይሆን?››(አሳዬ ደርቤ)እንዴት ዋላችሁ ምዕመናን? እኔ...
By Assaye 2017-11-12 13:09:47 0 0
Other
From Crisis to Comeback: How ORM Agencies Handle Online Attacks
In today’s digital-first world, a brand’s reputation can make or break its success....
By abhinavshina 2025-06-16 09:54:37 0 0
Uncategorized
Macaafa Qulqulluu!!
Ergaa jireenya dhugaa fi Amantii.
By T002 2017-11-15 04:43:20 0 0
Uncategorized
ወርቃማው ደብዳቤ !
(አሌክስ አብረሃም) እንዴት ናት ኢትዮጲያ እንዴት ነው አፈሩ ጤናቸው እንዴት ነው ጠቅላይ ሚንስትሩ ?ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህናናቸው...
By binid 2017-11-24 20:16:44 0 0
Uncategorized
Champion marathon runner Zenash Gezmu who fled Ethiopia found beaten to death by another refugee in Paris
A champion marathon runner who fled Ethiopia six years ago for a better life in Europe has been...
By rahwa 2017-12-01 07:24:35 0 0