ዘውዲቱ ሆስፒታል 5 የኩላሊት እጥበት መስጫ መሳሪያዎችን በወቅቱ አለመግዛቱ ችግር ፈጥሮብናል
ዘውዲቱ ሆስፒታል 5 የኩላሊት እጥበት መስጫ መሳሪያዎችን በወቅቱ አለመግዛቱ ችግር ፈጥሮብናል-ታካሚዎች
ዘውዲቱ ሆስፒታል ከአንድ ዓመት በፊት ለአምስት የኩላሊት እጥበት (ዲያሊስስ) መሳሪያዎች ግዥ የ1 ሚሊየን ብር ድጋፍ ቢያገኝም እስካሁን ግዥ አለመፈፀሙ ታካሚዎች ህክምናውን በቀላሉ እንዳናገኝ አድርጎናል የሚል ቅሬታ አቅርበዋል።
ከ300 በላይ ታካሚዎች የኩላሊት እጥበት አገልግሎት ለማግኘት በሆስፒታሉ ወረፋ የሚጠብቁ ሲሆን፥ አሁን ላይ ያሉት አምስት የኩላሊት እጥበት ወይም የዲያሊስስ መስጫ ማሽኖች በቀን በአማካይ ለ25 ታካሚዎች አገልግሎት እየሰጡ ነው።
ሆስፒታሉ ተጨማሪ አምስት የኩላሊት እጥበት መሳሪያዎች ለመግዛት...