ዘውዲቱ ሆስፒታል 5 የኩላሊት እጥበት መስጫ መሳሪያዎችን በወቅቱ አለመግዛቱ ችግር ፈጥሮብናል

0
0

ዘውዲቱ ሆስፒታል 5 የኩላሊት እጥበት መስጫ መሳሪያዎችን በወቅቱ አለመግዛቱ ችግር ፈጥሮብናል-ታካሚዎች

ዘውዲቱ ሆስፒታል ከአንድ ዓመት በፊት ለአምስት የኩላሊት እጥበት (ዲያሊስስ) መሳሪያዎች ግዥ የ1 ሚሊየን ብር ድጋፍ ቢያገኝም እስካሁን ግዥ አለመፈፀሙ ታካሚዎች ህክምናውን በቀላሉ እንዳናገኝ አድርጎናል የሚል ቅሬታ አቅርበዋል።

ከ300 በላይ ታካሚዎች የኩላሊት እጥበት አገልግሎት ለማግኘት በሆስፒታሉ ወረፋ የሚጠብቁ ሲሆን፥ አሁን ላይ ያሉት አምስት የኩላሊት እጥበት ወይም የዲያሊስስ መስጫ ማሽኖች በቀን በአማካይ ለ25 ታካሚዎች አገልግሎት እየሰጡ ነው።

ሆስፒታሉ ተጨማሪ አምስት የኩላሊት እጥበት መሳሪያዎች ለመግዛት ከባምቢስ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ ከአንድ ዓመት በፊት ማግኘቱ ይታወሳል።

በመሳሪያዎች ቁጥር ተገድበው ተራቸውን የሚጠብቁ የኩላሊት ታካሚዎች ግን ዘውዲቱ ሆስፒታል ላይ ቅሬታ ያሰማሉ።

ከአንድ ዓመት በፊት አምስት የኩላሊት እጥበት መሳሪያዎችን እንዲያስገባ 1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ቢያገኝም፥ እስካሁን ግዥውን አልፈጸመም፤ በዚህም ህክምናውን በቀላሉ ማግኘት አልቻልንም ነው ያሉት።

የመሳሪያዎች ግዥ በወቅቱ አለመፈጸሙ ሆስፒታሉ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚያገኙ ዜጎች ቁጥርን በእጥፍ ያሳድግ ነበር።

ችግሩን መኖሩን የሚያምነው ዘውዲቱ ሆስፒታል በበኩሉ፥ በድጋፍ የተገኘው ገንዘብ ለአምስት የኩላሊት እጥበት መሳሪያዎች ግዥ እንደማይበቃ በአስመጪዎች በኩል ስለተነገረን አማራጭ መፈለጉ ጊዜ ወስዷል ብሏል።

በሆስፒታሉ የኩላሊት ስፔሻሊስት ዶክተር ተስፋዬ ይልማ፥ ግዥው በአስመጪዎች በኩል ቢያለፍ ገንዘቡ መሳሪያዎቹን እንደማይገዛ ከተነገረን ወዲህ ሆስፒታሉ በልዩ ፈቃድ ራሱ እንዲያስገባ መፈቀዱን ተናግረዋል።

የተጠየቀው ፈቃድ ቢገኝም የብር የመግዛት አቅም መዳከም ደግሞ ሌላ ችግር እንደፈጠረባቸው ነው የገለፁት።

ዶክተር ተስፋዬ የተጨመረው 450 ሺህ ብር ከመንግስት ማግኘት ቀላል ቢሆንም፥ ለሆስፒታሉ የተፈቀደው ልዩ ግዥ ያንን አካሄድ እንደማይፈቅድ ይጠቅሳሉ።

ከባምቢስ ሃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር ባለፈው ዓመት የተገኘው የአንድ ሚሊዮን ብር፥ ድጋፍ አሁን ላይ በሮተሪ ክለብ የእርዳታ ድርጅት እጅ እንደሚገኝ የድርጅቱ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ መላኩ በዛ ገልፀዋል።

ለግዥው መዘግየትም የሆስፒታሉ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት መጓተቱን እንጂ ችግሩ አሳሳቢ ባለመሆኑ የመጣ አይደለም ነው ያሉት።

በሌላ በኩል ሞት በኩላሊት ይብቃ በጎ አድራጎት ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ እዮብ ተወልደ መድህን፥ የገንዘብ ድጋፉ የተገኘው በማህበሩ ተደጋጋሚ ጥያቄ ነው፤ ብሩ ቢፈቀድልን ማሽኑን ያለቀረጥ እንድናሰገባ የመንግስት ድጋፍ አለን ይላሉ።

በወቅቱ የሮተሪ ክለብ ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ መላኩ በበኩላቸው፥ ድጋፉ ለዘውዲቱ ሆስፒታል እንጂ ከማህበሩ ጋር አይገናኝም ብለዋል።

አሁን ላይ ዘውዲቱ ሆስፒታል ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ በማፈላለግ በተፈቀደው ግዥ ወይም በመንግስት የግዥ አካሄድ መሳሪያዎችን ለማስገባት ጥረት እያደረገ መሆኑን ዶከተር ተሰፋዬ ጠቁመዋል።

በንብረቴ ተሆነ

Search
Categories
Read More
Uncategorized
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)(ማስጠንቀቂያ….ይህ ጽሁፍ ልክ እንደ እሁድ ረዥም ስለሆነ ስራ ያለበት ሰው ከእሁድ ውጪ...
By Andualem Buketo 2017-11-12 15:13:23 0 0
Uncategorized
የመጀምሪያዋ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጦር መርከብ ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም ከመያዟ በፊት P.C. 1616 ትባል ነበር። ይህች ዘመናዊ መርከብ ከአሜሪካን መንግስት በእርዳታ የተገኘች ነበረች።
1616 ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም እንዲወጣላት በማስፈለጉ በጊዜው የነበረውን ተጨባጭ ሁ...
By Dagmawisol 2017-12-16 09:06:27 0 0
Uncategorized
The story behind the arrest of Mohammed Ali Al-Amoudi explained (Gossip)
The first troubling signs that Mohammed Ali Al-Amoudi (Sheikh) may, after all, have faced trying...
By Rahwa teklu 2017-11-13 16:15:40 1 0
Uncategorized
_ ጥሩነት ለራስ ነው:: __
ሥራ ፈላጊው ለሥራ ውድድር የቃል መጠይቅ ፈተና ለመውሰድ መስሪያ ቤት ላይ ተገኝቷል፡፡ ኮሪደር ላይ ሆኖ የፈተና ጊዜውን ሲጠባበቅ ሳለ የወዳደቁ ቁርጥራጭ...
By Samri mola 2017-11-25 09:01:10 0 0
Uncategorized
ሴቶች ለምን እንዲሁ ያለቅሳሉ __
 ሴቶች ለምን እንዲሁ ያለቅሳሉ __ ትንሹ ልጅ እናቱን “ማሚ ለምን ታለቅሻለሽ?” ሲል ጠየቃት “ምክንያቱም...
By Dagmawisol 2017-11-17 07:15:51 0 0