የሂዝቦላ መሪ ተገደሉ
የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሂዝቦላ መሪ ሃሰን ናስረላህን በቤሩት ባካሄደው የአየር ጥቃት መግደሉን የእስራኤል ጦር አስታወቀ፡፡
የእስራኤል ወታደራዊ ቃል አቀባይ ሌተናንት ኮሎኔል ናዳቭ በቀድሞ አጠራሩ ትዊተር ተብሎ በሚታወቀው የኤክስ ገጻቸው ላይ ባወጡት ጽሁፍ ነው የሃሰን ናስርላህን መገደል ያስታወቁት፡፡
ሌላው የእስራኤል ቃል አቀባይ ካፒቴን ዴቪድ አቭራሃም ትላንት ዓርብ በሊባኖስ ዋና ከተማ ላይ የተካሄደውን ጥቃት ተከትሎ የሂዝቦላ መሪ “ተወግዷል” ሲሉ ለአጃንስ...