ዩናይትድ ስቴትስ ሶሪያ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 37 ታጣቂዎች ተገደሉ
ዩናይትድ ስቴትስ በሶሪያ ታጣቂዎች ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ከአልቃይዳ እና እስላማዊ መንግሥት (አይ ኤስ) የሽብር ቡድን ጋር ግንኙት ያላቸው 37 ታጣቂዎችን መግደሏን የዩናይትድ ስቴትስ ጦር አስታወቀ።
ከሟቾቹ መካከል ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮች እንደነበሩ ተገልጿል።
ባለፈው ማክሰኞ በሰሜን ምዕራብ ሶሪያ ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ማዕከላዊ ዕዝ በፈጸመው ጥቃት፤ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያለው ሁራስ አል-ዲን ቡድንንና ሌሎች ስምንት ከፍተኛ ታጣቂዎች ዒላማ...