ኢትዮጵያ እና አይ ኤም ኤፍ በገንዘብ ድጋፍ ዙርያ ተስማሙ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ ሠራተኞች እና የኢትዮጵያ መንግስት የአራት-ዓመት 3.4 ቢሊዮን ዶላር የብድር ዝግጅት የመጀመሪያ ግምገማ ለማጠናቀቅ በሚያስችሉ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን አይ ኤም ኤፍ ትላንት ዓርብ አስታወቀ።
ግምገማው ሲጠናቀቅ "ኢትዮጵያ ወደ 345 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የገንዘብ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል" ሲልም አይ ኤም ኤፍ ገልጿል።
ስምምነቱ የተቋሙን አስተዳደር እና የስራ አስፈፃሚ ቦርድ ይሁንታ...