የብሪታንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፑቲንን ዛቻ አጣጣሉ
የብሪታንያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴቪድ ላሚ ዛሬ እሁድ በሰጡት አስትያየት ዩክሬን ከሩሲያ ምድር ዘልቆ ጉዳት የማድረስ አቅም ያለው የረዥም ርቀት መሳሪያ እንድትጠቀም መፍቀድ ኔቶን ከሞስኮ ጋር ከለየለት ጦርነት ውስጥ ያስገባታል በሚል የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለሰነዘሩት ማስጠንቀቂያ “በመደንፋት” ወንጅለዋቸዋል።
የዩናይትድ ስቴት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር በዋይት ሀውስ ተገናኝተው ኪየቭ ከምዕራቡ ዓለም...