በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ሊካሄድ የነበረው ሶስተኛው ዙር ውይይት ለሌላ ጊዜ ተላለፈ
ውይይቱ ለሌላ ጊዜ የተላለፈው በኒውዮርክ ከሚካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ጋር በመገጣጠሙ ምክንያት መሆኑን ሁለት የሶማሊያ ከፍተኛ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
ስለጉዳዩ ለመገናኛ ብዙሃን ለመናገር ፈቃድ ስለሌላቸው ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁት አንደኛው የሶማሊያ ባለስልጣን የውይይቱ ጊዜ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ጉዞ እና ዝግጅት ጋር መገጣጠሙ ተናግረዋል። ሁለተኛው ባለስልጣን በበኩላቸው ለውይይቱ ለመዘጋጀት ያለው ጊዜ...