በደቡብ ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ክፍያ መቅረት እና ያስከተለው ቀውስ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ስለማይከፈላቸው አንዳንድ መምህራን የተማሩባቸውና ሲያገለግሉበት የነበረውን ሞያ ትተው በግብርና ሥራ መሰማራታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ::
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ውስጥ በሚገኙ 21 ወረዳዎች ተቀጥረው በማገልገል ላይ የነበሩ የመንግሥት ሠራተኞች የወር ደሞዛቸው ለረዥም ጊዜ በመቁረጡ ለኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ችግሮች ተጋለጣቸውን አስረድተዋል::
በዳሞት ወይዴ ወረዳ ብቻ ከ3ሺህ በላይ...