የዴሞክራቶች ጉባኤ ካማላ ሃሪስ የፓርቲያቸው እጩ ሆነው መመረጣቸውን በሚቀበሉበት ሥነ ስርአት ዛሬ ይጠናቀቃል
አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የዴሞክራቶች ጉባኤ የዩናይድ ስቴትሷ ምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ ታሪካዊ በሆነ ሂደት በፕሬዝዳንታዊው የምርጫ ፉክክር የፓርቲያቸው እጩ ሆነው የተሰየሙበትን ውሳኔ በሚቀበሉበት ሥነ ስርአት ዛሬ ምሽት ይጠናቀቃል።
በሥነ ስርአቱም ሃሪስ ለሃገራቸው ያላቸውን ራዕይ ይፋ በማድረግ፤ ከሪፐብሊካኑ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ የተሻሉ አማራጭ የሚሆኑበትን ምክኒያት ያሳያሉ።
በዚህም የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የዳግም ምርጫ ዘመቻ አክትሞ በምትካቸው ሃሪስ...