ጄክ ሰለቨን ከቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ይነጋገራሉ
የዩናይት ስቴትስ ብሄራዊ የደህንነት አማካሪ ጄክ ሰለቨን ከቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋን ዪ ጋር ለመነጋገር በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ቻይና እንደሚጓዙ ስለ ጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ተናገሩ፡፡
ንግግሩ በዚህ ዓመት መጨረሻ በፕሬዝዳንት ባይደን እና በቻይናው አቻቸው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ መካከል ሊደረግ የሚችለውንም ስብሰባ ያካትታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የታቀዱት ስብሰባዎች የአሜሪካ-ቻይና ግንኙነቶችን ለማረጋጋት በተከታታይ ከታቀዱት የከፍተኛ ደረጃ...