ቲም ዋልዝ እጩነታቸውን በይፋ ተቀበሉ
የሜንሶታው አገረ ገዥ ቲም ዋልዝ የዲሞክራቲክ ፓርቲውን በመወከል ለምክትል ፕሬዝደንትነት እንዲወዳደሩ መታጨታቸውን እንደተቀበሉ ረቡዕ ምሽት ቺካጎ ላይ በቀጠለው የፓርቲው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ አስታውቀዋል።
“ለአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንትነት እንደወዳደር በእጩነት መምረጣችሁን ስቀበል በሕይወቴ ትልቅ ክብር ይሰማኛል” ብለዋል ቲም ዋልዝ።
“በእኔ ላይ እምነት በመጣላችሁ አመሰግናለሁ” ብለዋል ቲም ዋልዝ። በእጩነት ያቀርቧቸውንና ፕሬዝደንታዊ እጩ የሆኑትን ካመላ...