ሄዝቦላ ከ50 በላይ ተጨማሪ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል አስወነጨፈ
የሌባኖሱ ሄዝቦላ ከሃምሳ የሚበልጡ ሮኬቶችን ዛሬ ወደ እስራኤል ያስወነጨፈ ሲሆን፣ እስራኤል ወደ ግዛቷ በቀላቀለችው ጎላን ሃይትስ በሚገኙ በርካታ የግል መኖሪያ ቤቶች ላይ አርፏል።
ጥቃቱ የመጣው በጋዛው ጦርነት የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ከግብፅ እና ቃጣር አደራዳሪዎች ጋራ በተገናኙ ማግስት ነው።
የተኩስ አቁም ላይ ለመድረስ አሁንም አንዳንድ ችግሮች እንዳሉ እስራኤልም ሆነች ሐማስ በማስታወቅ ላይ ናቸው።
አዲስ የቀረበው...