ምርጫ ቦርድ በተጭበረበረ ሰነድ ለህወሓት እውቅና ሰጥቷል ሲሉ አቶ ጌታቸው አቤቱታ አቀረቡ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ(ህ.ወ.ሓ.ት)፣ ትላንት “በልዩ ኹኔታ” የሰጠው የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ፣ በተጭበረበረ ሰነድ ላይ ተመስርቶ መኾኑን ገልጸው ለምርጫ ቦርድ አቤቱታ አቀረቡ።
ህወሓት በበኩሉ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ፣ ምርጫ ቦርድ የሰጠው ውሳኔ ፓርቲው ካቀረበው ጥያቄ ጋራ የማይገናኝ እና ድርጅቱ ሕጋዊ ሰውነቱ...