በሶማሊያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር አንድ ወታደራዊ ሠፈርን አስረከበ
በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ በመሆን በሶማሊያ የተሰማራው የኢትዮጵያ ጦር ከያዛቸው ወታደራዊ ሠፈሮች ውስጥ ማሃስ በተሰኘችው ከተማ ያለውን ሠፈር ዛሬ ለሶማሊያ ኃይሎች አስረክቧል።
ሂራን በተባለ ክልል፣ ከበለደወይን ከተማ 120 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የሚገኘውና ዛሬ ለሶማሊያ ኃይሎች ተላልፎ የተሰጠው የጦር ሰፈር፣ የአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ጦሩን ደረጃ በደረጃ ለመቀነስ ባካሄደው ሶስተኛ ዙር የተፈጸመና፣ ለሶማሊያ ኃይሎች ተላልፎ የተሰጠ ስድስተኛው ወታደራዊ ሠፈር...