• #ethiopia
    #ethiopia
    ALLAFRICA.COM
    Somalia: President Farmajo Cuts Short Ethiopia Visit
    President of Somalia, Mohamed Abdullahi Mohamed Farmajo, on Wednesday, said he was cutting an official visit to neighbouring Ethiopia in order to return and participate in the burial of the youngest minister in his government.
    0 Comments 0 Shares
  • KEFI Minerals inks Tulu Kapi agreement with Ethiopia government
    KEFI Minerals said subsidiary KEFI Minerals (Ethiopia) Ltd (KME) and the Federal Democratic Republic of Ethiopia have signed the shareholders' agreement for the incorporation, ownership and operation of Tulu Kapi Gold Mines Share Company Ltd (TKM).
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.GOOGLE.COM
    Ethiopia: Refugee Influx Into Ethiopia - Challenges & Solutions
    Opinion - The IGAD region hosts 2.46 million refugees, while also producing 3.12 million refugees. Ethiopia shelters 33 percent of the total number of refugees in the IGAD region and 2.3 percent of the total number of refugees world-wide, while producing 0.5 percent of the world's total number of refugees, thus caring for more than its share of the global refugee burdens. The list also includes 20,000 refugees residing in Addis Ababa for reasons related to special medical attention, humanitarian issues and serious p
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በአለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ወርሃዊ የሀገራት ደረጃ ኢትዮጵያ በነበረችበት 124ኛ ላይ ተቀመጠች።

    ወርሃዊው የፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ ይፋ ሆኗል።

    ኢትዮጵያ ባላፈው ወር 20 ደረጃዎችን ማሽቆልቆሏ የሚታወስ ነው፡፡

    ፊፋ ባወጣው የወሩ ደረጃም ብራዚል፣ አርጀንቲና እና ጀርመን ካለፈው ወር የደረጃ ለውጥ ሳያደርጉ ባሉበት በቅደም ተከተል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

    ከአፍሪካ ግብፅ ቀዳሚ ስትሆን ሴኔጋል እና የወቅቱ የአፍሪካ ሻምፒዮን ካሜሩን ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል።

    የአፍካ መሪዎቹ ሀገራት ከዓለም በደረጃቸው ቅደም ተከተል መሰረት 19ኛ፣ 30ኛ፣ 33ኛ ላይ ይገኛሉ፡፡

    በወሩ ማላዊ 14 ደረጃዎችን በማሽቆልቆል ቀዳሚዋ ስትሆን 114ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

    ከፍተኛ የደረጃ ማሻሻል ያሳዩ ሀገራት ደግሞ ማዳጋስካር 9 ደረጃዎችን በማሻሻል 111ኛ፣ ደቡብ ሱዳን 7 ደረጃዎችን በማሻሻል 146ኛ ደረጃን መያዛቸው በመረጃው ተጠቅሷል።

    በደረጃው ግርጌ ላይ ደግሞ አንጉይላ፣ ባህማስ፣ ኤርትራ፣ ጂብራልተር፣ ሶማሊያ እና ቶንጋ ያለምንም ነጥብ 206ኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን ከፊፋ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
    አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በአለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ወርሃዊ የሀገራት ደረጃ ኢትዮጵያ በነበረችበት 124ኛ ላይ ተቀመጠች። ወርሃዊው የፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ ይፋ ሆኗል። ኢትዮጵያ ባላፈው ወር 20 ደረጃዎችን ማሽቆልቆሏ የሚታወስ ነው፡፡ ፊፋ ባወጣው የወሩ ደረጃም ብራዚል፣ አርጀንቲና እና ጀርመን ካለፈው ወር የደረጃ ለውጥ ሳያደርጉ ባሉበት በቅደም ተከተል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ከአፍሪካ ግብፅ ቀዳሚ ስትሆን ሴኔጋል እና የወቅቱ የአፍሪካ ሻምፒዮን ካሜሩን ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል። የአፍካ መሪዎቹ ሀገራት ከዓለም በደረጃቸው ቅደም ተከተል መሰረት 19ኛ፣ 30ኛ፣ 33ኛ ላይ ይገኛሉ፡፡ በወሩ ማላዊ 14 ደረጃዎችን በማሽቆልቆል ቀዳሚዋ ስትሆን 114ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ ከፍተኛ የደረጃ ማሻሻል ያሳዩ ሀገራት ደግሞ ማዳጋስካር 9 ደረጃዎችን በማሻሻል 111ኛ፣ ደቡብ ሱዳን 7 ደረጃዎችን በማሻሻል 146ኛ ደረጃን መያዛቸው በመረጃው ተጠቅሷል። በደረጃው ግርጌ ላይ ደግሞ አንጉይላ፣ ባህማስ፣ ኤርትራ፣ ጂብራልተር፣ ሶማሊያ እና ቶንጋ ያለምንም ነጥብ 206ኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን ከፊፋ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
    0 Comments 0 Shares
  • በዩሮፓ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጭ አሸንፏል

    አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 27 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት ምሽት በተደረገ የዩሮፓ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ አንድ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ ባለድል ሆኗል።
    በባላይዶስ ስታዲየም የስፔኑ ሴልታቪጎ ከማንቼስተር ዩናይትድ ተጫውተዋል።
    በሳምንቱ መጨረሻ ከአትሌቲክ ቢልባኦ ባደረጉት ጨዋታ፥ በርካታ ተጫዋቾቻቸውን አሳርፈው ወደ ሜዳ የገቡት ሴልታቪጎዎች ያሰቡትን አላሳኩም።
    ማንቼስተር ዩናይትዶች በመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ መንቀሳቀስ እና የጎል እድሎችን መፍጠር ቢችሉም ያገኙትን አጋጣሚ መጠቀም አልቻሉ።
    በዚህ የጨዋታ ጊዜ ወጣቱ አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ ከሳጥን ውጭ የግቡ ማዕዘን ላይ የመታት ኳስ በእለቱ ኮከብ በነበረው ግብ ጠባቂ ሰርጅዮ አልቫሬዝ ጥረት ከሽፋለች።
    ከዚህ ባለፈም አማካዮቹ ሄንሪክ ሚኪታሪያን እና ጀሴ ሌንጋርድ ያገኟቸውን አጋጣሚዎች ወደ ጎል መቀየር አልቻሉም።
    ግብ ጠባቂው በመጀመሪያ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ሶስት ኳሶችን ማዳን ችሏል።
    በአንጻሩ ሴልታቪጎዎች በዚህ የጨዋታ ጊዜ የሚያስቆጭ የጎል እድል መፍጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።
    አማካዩ ዋስ ከመሃል የተሻገረለትን ኳስ ነጻ ሆኖ ቢያገኘውም ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
    ከእረፍት መልስ ባለሜዳዎቹ የተሻለ ወደ ጎል መቅረብ ቢችሉም ያሰቡትን ማሳካት አልቻሉም።
    በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫ የተወሰደባቸው ማንቼስተር ዩናይትዶች በራሽፎርድ የ67ኛው ደቂቃ ጎል ጨዋታውን 1 ለ 0 መምራት ችለዋል።
    ከዚህ በኋላ ተጨማሪ ጎል ሳይቆጠር ዩናይትድ በዚህ አመት ያደረገውን 58ኛ ጨዋታ በድል መወጣት ችሏል።
    የመልሱ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት ኦልድትራፎርድ ላይ ተደርጎ በደርሶ መልስ አሸናፊው በግንቦት ወር አጋማሽ ለሚደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ይቀርባል።
    ከትናንት በስቲያ በተደረገ ጨዋታ አምስተርዳም አሬና ላይ አያክስ አምስተርዳም ኦሎምፒክ ሊዮንን 4 ለ 1 ማሸነፉ ይታወሳል።
    በዩሮፓ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጭ አሸንፏል አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 27 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት ምሽት በተደረገ የዩሮፓ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ አንድ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ ባለድል ሆኗል። በባላይዶስ ስታዲየም የስፔኑ ሴልታቪጎ ከማንቼስተር ዩናይትድ ተጫውተዋል። በሳምንቱ መጨረሻ ከአትሌቲክ ቢልባኦ ባደረጉት ጨዋታ፥ በርካታ ተጫዋቾቻቸውን አሳርፈው ወደ ሜዳ የገቡት ሴልታቪጎዎች ያሰቡትን አላሳኩም። ማንቼስተር ዩናይትዶች በመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ መንቀሳቀስ እና የጎል እድሎችን መፍጠር ቢችሉም ያገኙትን አጋጣሚ መጠቀም አልቻሉ። በዚህ የጨዋታ ጊዜ ወጣቱ አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ ከሳጥን ውጭ የግቡ ማዕዘን ላይ የመታት ኳስ በእለቱ ኮከብ በነበረው ግብ ጠባቂ ሰርጅዮ አልቫሬዝ ጥረት ከሽፋለች። ከዚህ ባለፈም አማካዮቹ ሄንሪክ ሚኪታሪያን እና ጀሴ ሌንጋርድ ያገኟቸውን አጋጣሚዎች ወደ ጎል መቀየር አልቻሉም። ግብ ጠባቂው በመጀመሪያ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ሶስት ኳሶችን ማዳን ችሏል። በአንጻሩ ሴልታቪጎዎች በዚህ የጨዋታ ጊዜ የሚያስቆጭ የጎል እድል መፍጠር ሳይችሉ ቀርተዋል። አማካዩ ዋስ ከመሃል የተሻገረለትን ኳስ ነጻ ሆኖ ቢያገኘውም ሳይጠቀምበት ቀርቷል። ከእረፍት መልስ ባለሜዳዎቹ የተሻለ ወደ ጎል መቅረብ ቢችሉም ያሰቡትን ማሳካት አልቻሉም። በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫ የተወሰደባቸው ማንቼስተር ዩናይትዶች በራሽፎርድ የ67ኛው ደቂቃ ጎል ጨዋታውን 1 ለ 0 መምራት ችለዋል። ከዚህ በኋላ ተጨማሪ ጎል ሳይቆጠር ዩናይትድ በዚህ አመት ያደረገውን 58ኛ ጨዋታ በድል መወጣት ችሏል። የመልሱ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት ኦልድትራፎርድ ላይ ተደርጎ በደርሶ መልስ አሸናፊው በግንቦት ወር አጋማሽ ለሚደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ይቀርባል። ከትናንት በስቲያ በተደረገ ጨዋታ አምስተርዳም አሬና ላይ አያክስ አምስተርዳም ኦሎምፒክ ሊዮንን 4 ለ 1 ማሸነፉ ይታወሳል።
    0 Comments 0 Shares
  • 27ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ነገ በሁለት ጨዋታዎች ቀጥሎ ይውላል

    አዲስ አበባ በ፣ ሚያዚያ 27 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) 27ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ነገ በሁለት ጨዋታዎች ቀጥሎ ይውላል።
    በርካታ ተመልካቾችን ወደ ሜዳ የሳበው የዘንድሮው አመት ፕሪሚየር ሊግ ሊጠናቀቅ የአራት ሳምንታት መርሃ ግብሮች ብቻ ይቀሩታል።
    ነገ በአዲስ አበባ ስታዲየም ሁለት ጨዋታዎች ሲደረጉ፥ 8 ሰዓት ከ30 ላይ መከላከያ ከድሬዳዋ ከተማ ይገናኛሉ።
    10 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ በ24 ነጥብ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን ያስተናግዳል።
    ፕሪሚየር ሊጉ እሁድ ሲቀጥል በአዲስ አበባ ስታዲየም 8 ሰዓት ከ30 ደደቢት ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ።
    በሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ 10 ሰዓት ከ30 ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ቡና ይገናኛሉ።
    በክልል ከተሞች ደግሞ አርባ ምንጭ ከተማ በሜዳው አዳማ ከተማን ሲያስተናግድ፥ ሃዋሳ ከተማ ከወልዲያ ከተማ ይጫወታሉ።
    ጅማ ላይ ደግሞ ጅማ አባቡና የሊጉን መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚገጥምበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
    የ27ኛው ሳምንት መርሃ ግብር የመጨረሻ ጨዋታ ሰኞ በአዲስ አበባ ከተማና ወላይታ ዲቻ መካከል በአዲስ አበባ ስታዲየም ይደረጋል።
    ሊጉን አንድ ቀሪ ጨዋታ ያለው ቅዱስ ጊዮርጊሰ በ49 ነጥብ ይመራዋል፥ ሲዳማ ቡና በ46 እንዲሁም ደደቢት በ45 ነጥቦች ይከተላሉ።
    ድሬዳዋ ከተማ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና አዲስ አበባ ከተማ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ።

    በዘላለም ተፈሪ
    27ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ነገ በሁለት ጨዋታዎች ቀጥሎ ይውላል አዲስ አበባ በ፣ ሚያዚያ 27 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) 27ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ነገ በሁለት ጨዋታዎች ቀጥሎ ይውላል። በርካታ ተመልካቾችን ወደ ሜዳ የሳበው የዘንድሮው አመት ፕሪሚየር ሊግ ሊጠናቀቅ የአራት ሳምንታት መርሃ ግብሮች ብቻ ይቀሩታል። ነገ በአዲስ አበባ ስታዲየም ሁለት ጨዋታዎች ሲደረጉ፥ 8 ሰዓት ከ30 ላይ መከላከያ ከድሬዳዋ ከተማ ይገናኛሉ። 10 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ በ24 ነጥብ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን ያስተናግዳል። ፕሪሚየር ሊጉ እሁድ ሲቀጥል በአዲስ አበባ ስታዲየም 8 ሰዓት ከ30 ደደቢት ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ። በሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ 10 ሰዓት ከ30 ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ቡና ይገናኛሉ። በክልል ከተሞች ደግሞ አርባ ምንጭ ከተማ በሜዳው አዳማ ከተማን ሲያስተናግድ፥ ሃዋሳ ከተማ ከወልዲያ ከተማ ይጫወታሉ። ጅማ ላይ ደግሞ ጅማ አባቡና የሊጉን መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚገጥምበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የ27ኛው ሳምንት መርሃ ግብር የመጨረሻ ጨዋታ ሰኞ በአዲስ አበባ ከተማና ወላይታ ዲቻ መካከል በአዲስ አበባ ስታዲየም ይደረጋል። ሊጉን አንድ ቀሪ ጨዋታ ያለው ቅዱስ ጊዮርጊሰ በ49 ነጥብ ይመራዋል፥ ሲዳማ ቡና በ46 እንዲሁም ደደቢት በ45 ነጥቦች ይከተላሉ። ድሬዳዋ ከተማ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና አዲስ አበባ ከተማ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ። በዘላለም ተፈሪ
    0 Comments 0 Shares
  • ከ2005 በፊት የተመዘገቡ የአለም ሪከርዶች ሊሰረዙ ይችላሉ መባሉ አግባብ አይደለም - አትሌት ቀነኒሳ
    ከ2005 በፊት የተመዘገቡ የአለም ሪከርዶች ሊሰረዙ ይችላሉ መባሉ አግባብ አይደለም - አትሌት ቀነኒሳ
    туристический онлайн-справочник
    Лучшие Андроид планшеты
    አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2005 በፊት የተመዘገቡ የአለም ሪከርዶች እንዲሰረዙ ለአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ጥያቄ ማቅረቡ ይታወሳል።

    ከ2005 በፊት የተመዘገቡት ሪከርዶች የሽንትና የደም ናሙና በማይሰበሰብበት ዘመን የተሰበሩ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ምናልባትም የአበረታች መድሃኒት ተጠቅመው በተወዳደሩ አትሌቶች የተሰበሩ ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ነው የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር ጥያቄውን ያቀረበው።


    የአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በመጪው ሰኔ ወር በሚያደርገው ጠቅላላ ጉባኤም ይህንኑ ጥያቄ ሊያጸድቀው እንደሚችል መገመቱን ተከትሎ የተለያዩ አትሌቶች ከወዲሁ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው።

    በ2004 የ5 ሺህ ሜትርን በ2005 ደግሞ የ10 ሺህ ሜትርን ሪከርድ ያስመዘገበው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው አስተያየት፥ እንደ አውሮፓውያኑ ከ2005 በፊት የተሰበሩ የአለም ሪከርዶች የሽንት እና የደም ናሙና ባልተወሰደበት ጊዜ የተመዘገቡ ናቸው በሚል ሪከርዶቹ ሊሰረዙ ይገባል መባሉ አግባብ አይደለም ብሏል።

    አትሌት ቀነኒሳ ችግሩ ከአለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የአሰራር ድክመት የመጣ እንጂ የአትሌቶች ችግር እንዳልሆነም ተናግሯል።

    ቀነኒሳ በጉዳዩ ዙሪያም ተቃውሞ ለማሰማት መዘጋጀቱን ነው ያስታወቀው።

    በ2003 የለንደን ማራቶን የአለም ሪከርድን ያስመዘገበችው እንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ከጋርዲያን ጋር ባደረገችው ቆይታ፥ ሪከርዶቹ ይሰረዙ የሚለው ሀሳብ ለቀድሞ አትሌቶች ክብር ከማጣት የመጣ ነው ብላለች።

    የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳያገኝም የራሷን ጥረት እንደምታደርግ አስታውቃለች።

    በእዩኤል ዘሪሁን
    ከ2005 በፊት የተመዘገቡ የአለም ሪከርዶች ሊሰረዙ ይችላሉ መባሉ አግባብ አይደለም - አትሌት ቀነኒሳ ከ2005 በፊት የተመዘገቡ የአለም ሪከርዶች ሊሰረዙ ይችላሉ መባሉ አግባብ አይደለም - አትሌት ቀነኒሳ туристический онлайн-справочник Лучшие Андроид планшеты አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2005 በፊት የተመዘገቡ የአለም ሪከርዶች እንዲሰረዙ ለአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ጥያቄ ማቅረቡ ይታወሳል። ከ2005 በፊት የተመዘገቡት ሪከርዶች የሽንትና የደም ናሙና በማይሰበሰብበት ዘመን የተሰበሩ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ምናልባትም የአበረታች መድሃኒት ተጠቅመው በተወዳደሩ አትሌቶች የተሰበሩ ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ነው የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር ጥያቄውን ያቀረበው። የአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በመጪው ሰኔ ወር በሚያደርገው ጠቅላላ ጉባኤም ይህንኑ ጥያቄ ሊያጸድቀው እንደሚችል መገመቱን ተከትሎ የተለያዩ አትሌቶች ከወዲሁ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው። በ2004 የ5 ሺህ ሜትርን በ2005 ደግሞ የ10 ሺህ ሜትርን ሪከርድ ያስመዘገበው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው አስተያየት፥ እንደ አውሮፓውያኑ ከ2005 በፊት የተሰበሩ የአለም ሪከርዶች የሽንት እና የደም ናሙና ባልተወሰደበት ጊዜ የተመዘገቡ ናቸው በሚል ሪከርዶቹ ሊሰረዙ ይገባል መባሉ አግባብ አይደለም ብሏል። አትሌት ቀነኒሳ ችግሩ ከአለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የአሰራር ድክመት የመጣ እንጂ የአትሌቶች ችግር እንዳልሆነም ተናግሯል። ቀነኒሳ በጉዳዩ ዙሪያም ተቃውሞ ለማሰማት መዘጋጀቱን ነው ያስታወቀው። በ2003 የለንደን ማራቶን የአለም ሪከርድን ያስመዘገበችው እንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ከጋርዲያን ጋር ባደረገችው ቆይታ፥ ሪከርዶቹ ይሰረዙ የሚለው ሀሳብ ለቀድሞ አትሌቶች ክብር ከማጣት የመጣ ነው ብላለች። የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳያገኝም የራሷን ጥረት እንደምታደርግ አስታውቃለች። በእዩኤል ዘሪሁን
    0 Comments 0 Shares
  • በእህቴ ሰርግ ላይ እንዴት እንደዛ ብለው
    ይዘፍናሉ.....?
    (አሌክስ አብርሃም ላላነበቡት ብቻ)

    እህቴ ስታገባ እቤታችን ሰርግ ተደግሶ
    ነበር፡፡ ያውም ድል ያለ ሰርግ ፡፡ ለመጀመሪያ
    ጊዜ በሰርግ የተደሰትኩት የዛን ጊዜ ነው ፡፡
    እህቴን ከነኮተቷ ከቤት የሚወስድ ጅል ሲገኝ
    እንዴት አልደሰትም!!
    የመንደሩ ሰው ሁሉ ..‹‹.እች ልጅ ቁማ መቅረቷ ነው?..›› እያለ ሲያማት እሷም በሙሉ ሃይሏ
    እየዘነጠችና እየተቆነጃጀች (ባል አጥቸ
    ሳይሆን የሚመጥነኝ ጠፍቶ ነው) አይነት ጉራ
    ቀመስ መልክት እያስተላለፈች
    ስትኖር ....በአንድ የተንሸዋረረ ቅዳሜ እህቴ
    ባል የሚሆናትን ልጅ አገኘች (ማነው ስሙ አሜሪካንን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲያገኝ እንደሷ
    አልተደሰተም)፡፡
    እንዴት እንደተገኛኙ ባይገባኝም ልክ በወጥመድ
    እንደተያዘ ወፍ አጣድፋ ትዳር የሚባል ትልቅ
    የብረት ድስት ውስጥ ከተተችው፡፡ እንደዜጋ
    ልጁ ቢያሳዝነኝም የእህቴም ችግር ይገባኛልና ‹‹ኧረ አስብበት›› ለማለት አልደፈርኩም፡፡
    ሰርጉ ተደገሰ ለእህቴ ሚዜ ለመሆን የአገር
    ሴቶች ተሰበሰቡ (አሁን ሚዜ መሆን ምን ያሻማል)
    እና ሰርጉ ደርሶ ሚዜ ተብየወቹ ነፍሳቸውን
    እስኪስቱ ዘንጠው በቀለም የጥምቀት ዱላ
    መስለው .. የገናም አባት መስለው... አበባ አንከርፍፈውና ተራቁተው እግረ ሚዜነታቸውን
    ለራሳቸው ከሰርገኛው መሃል ባል እየፈለጉ
    እያለ ሙሽራው መጣ (እኔማ ይቀራል ብየ ነበር
    የሚገርም ደፋር ነው)
    ከመጣም በኋላ ካሁን አሁን ‹‹ይሄ ነገር ሳስበው
    ቢቀርብኝ ይሻላል ›› ይላል እያልኩ ስሰጋ ....እነዛ ቀልቃላ ሚዜወቿ ‹‹አናስገባም
    ሰርገኛ›› ብለው እርፍ!!....እንዴዴዴዴዴ እች
    ልጅ ሚዜ ነው ምቀኛ የሰበሰበችው ብየ የመጨረሻ
    ተበሳጨሁ በአእርግጠኝነት ሙሽራው ‹‹ታዲያ የት
    ልግባ ቢል›› ሁሉም ሚዜወች ላዳ ተከራይተው
    እቤታቸው ነበር የሚወስዱት !! በስንት መከራ የተገኘ ባል ‹‹አናስገባም››! እኔ
    ወደፊት ስሞት መላአእክት ወደገነት
    ‹‹አናስገባም›› ቢሉኝ እራሱ እንደዚያ ቀን
    የምደነግጥ አይመስለኝም!! ይታያችሁ እህቴ ባል ለማግባት ለኪዳነ ምህረት
    ፣ለገብሬል ...ለማሪያም...የተሳለችው መጋረጃ
    ቢቀጣጠል አንድ ክፍለ ከተማ
    ይጋርዳል ....የተሳለችው ጧፍ የብዙ ደብሮችን
    የአመት የጧፍ ፍጆታ ይችላል...እና ሚዜወቿ
    ‹‹አናስገባም›› እያሉ በእሳት ይጫወታሉ !! አባባ በሩን ለሰርጉ ብሎ ሰፋ ያስደረገው ቶሎ
    ይዞልን እንዲሄድ አይደል እንዴ ! ወይ ሚዜ !
    ወይ ሴቶች ! ለሞላ ዘፈን
    ‹‹አናስገባም›› ....ቀስ ብየ ወደዲጀው ጠጋ
    አልኩና በጆሮው መፍትሄ ነገር ሹክ አልኩት
    ‹‹ኧረ አሌክስ ይሄማ አሁን አይከፈትም ሲወጠጡ ነው ›› አለኝ ...አትሸኟትም ወይ የሚለውን
    የፀጋየ እሸቱን የሰርግ ዘፈን ነበር ክፈትልን
    ያልኩት
    በእህቴ ሰርግ ላይ እንዴት እንደዛ ብለው ይዘፍናሉ.....? (አሌክስ አብርሃም ላላነበቡት ብቻ) እህቴ ስታገባ እቤታችን ሰርግ ተደግሶ ነበር፡፡ ያውም ድል ያለ ሰርግ ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰርግ የተደሰትኩት የዛን ጊዜ ነው ፡፡ እህቴን ከነኮተቷ ከቤት የሚወስድ ጅል ሲገኝ እንዴት አልደሰትም!! የመንደሩ ሰው ሁሉ ..‹‹.እች ልጅ ቁማ መቅረቷ ነው?..›› እያለ ሲያማት እሷም በሙሉ ሃይሏ እየዘነጠችና እየተቆነጃጀች (ባል አጥቸ ሳይሆን የሚመጥነኝ ጠፍቶ ነው) አይነት ጉራ ቀመስ መልክት እያስተላለፈች ስትኖር ....በአንድ የተንሸዋረረ ቅዳሜ እህቴ ባል የሚሆናትን ልጅ አገኘች (ማነው ስሙ አሜሪካንን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲያገኝ እንደሷ አልተደሰተም)፡፡ እንዴት እንደተገኛኙ ባይገባኝም ልክ በወጥመድ እንደተያዘ ወፍ አጣድፋ ትዳር የሚባል ትልቅ የብረት ድስት ውስጥ ከተተችው፡፡ እንደዜጋ ልጁ ቢያሳዝነኝም የእህቴም ችግር ይገባኛልና ‹‹ኧረ አስብበት›› ለማለት አልደፈርኩም፡፡ ሰርጉ ተደገሰ ለእህቴ ሚዜ ለመሆን የአገር ሴቶች ተሰበሰቡ (አሁን ሚዜ መሆን ምን ያሻማል) እና ሰርጉ ደርሶ ሚዜ ተብየወቹ ነፍሳቸውን እስኪስቱ ዘንጠው በቀለም የጥምቀት ዱላ መስለው .. የገናም አባት መስለው... አበባ አንከርፍፈውና ተራቁተው እግረ ሚዜነታቸውን ለራሳቸው ከሰርገኛው መሃል ባል እየፈለጉ እያለ ሙሽራው መጣ (እኔማ ይቀራል ብየ ነበር የሚገርም ደፋር ነው) ከመጣም በኋላ ካሁን አሁን ‹‹ይሄ ነገር ሳስበው ቢቀርብኝ ይሻላል ›› ይላል እያልኩ ስሰጋ ....እነዛ ቀልቃላ ሚዜወቿ ‹‹አናስገባም ሰርገኛ›› ብለው እርፍ!!....እንዴዴዴዴዴ እች ልጅ ሚዜ ነው ምቀኛ የሰበሰበችው ብየ የመጨረሻ ተበሳጨሁ በአእርግጠኝነት ሙሽራው ‹‹ታዲያ የት ልግባ ቢል›› ሁሉም ሚዜወች ላዳ ተከራይተው እቤታቸው ነበር የሚወስዱት !! በስንት መከራ የተገኘ ባል ‹‹አናስገባም››! እኔ ወደፊት ስሞት መላአእክት ወደገነት ‹‹አናስገባም›› ቢሉኝ እራሱ እንደዚያ ቀን የምደነግጥ አይመስለኝም!! ይታያችሁ እህቴ ባል ለማግባት ለኪዳነ ምህረት ፣ለገብሬል ...ለማሪያም...የተሳለችው መጋረጃ ቢቀጣጠል አንድ ክፍለ ከተማ ይጋርዳል ....የተሳለችው ጧፍ የብዙ ደብሮችን የአመት የጧፍ ፍጆታ ይችላል...እና ሚዜወቿ ‹‹አናስገባም›› እያሉ በእሳት ይጫወታሉ !! አባባ በሩን ለሰርጉ ብሎ ሰፋ ያስደረገው ቶሎ ይዞልን እንዲሄድ አይደል እንዴ ! ወይ ሚዜ ! ወይ ሴቶች ! ለሞላ ዘፈን ‹‹አናስገባም›› ....ቀስ ብየ ወደዲጀው ጠጋ አልኩና በጆሮው መፍትሄ ነገር ሹክ አልኩት ‹‹ኧረ አሌክስ ይሄማ አሁን አይከፈትም ሲወጠጡ ነው ›› አለኝ ...አትሸኟትም ወይ የሚለውን የፀጋየ እሸቱን የሰርግ ዘፈን ነበር ክፈትልን ያልኩት
    0 Comments 0 Shares