
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
እንደህዝብ የመከበር ልኩ!
(አሌክስ አብርሃም)
በዓለማችን የመንገደኞች ባቡር ታሪክ ፌርማታው ላይ በሰዓቱ በመድረስ የጃፖኖችን ባቡር የሚወዳደር የለም!! በጃፖን "ባቡር ዘገየ" የሚል ወሬ ዜና ሁሉ ሊሆን ይችላል!!
ታዲያ መንገደኞች ቁመው ሲጠብቁ ባቡሩ (በምንም ምክንያት ) ከአንድ እሰከ አምስት ደቂቃ ከዘገየ መንገደኞች ከተሳፈሩ በኃላ የባቡሩ ሰራተኞች ሃላፊ ይቅርታ ይጠይቃል!! መንገደኛውን ባጠቃላይ በድምፅ ማጉያ መሠላችሁ??? በእያንዳንዱ መንገደኛ ወንበር እየሄደ ከወገቡ ሰበር ብሎ!!
የሚገርመው ይሄ አይደለም .... ባቡሩ ከአምስት ደይቃ በላይ አንድ ደይቃ እንኳን ቢዘገይ ለእያንዳንዱ ተሳፋሪ ማህተም ያለበት የይቅርታ ደብዳቤ ይሠጣል!! ይሉናል!እንደህዝብ የመከበር ልኩ! (አሌክስ አብርሃም) በዓለማችን የመንገደኞች ባቡር ታሪክ ፌርማታው ላይ በሰዓቱ በመድረስ የጃፖኖችን ባቡር የሚወዳደር የለም!! በጃፖን "ባቡር ዘገየ" የሚል ወሬ ዜና ሁሉ ሊሆን ይችላል!! ታዲያ መንገደኞች ቁመው ሲጠብቁ ባቡሩ (በምንም ምክንያት ) ከአንድ እሰከ አምስት ደቂቃ ከዘገየ መንገደኞች ከተሳፈሩ በኃላ የባቡሩ ሰራተኞች ሃላፊ ይቅርታ ይጠይቃል!! መንገደኛውን ባጠቃላይ በድምፅ ማጉያ መሠላችሁ??? በእያንዳንዱ መንገደኛ ወንበር እየሄደ ከወገቡ ሰበር ብሎ!! የሚገርመው ይሄ አይደለም .... ባቡሩ ከአምስት ደይቃ በላይ አንድ ደይቃ እንኳን ቢዘገይ ለእያንዳንዱ ተሳፋሪ ማህተም ያለበት የይቅርታ ደብዳቤ ይሠጣል!! ይሉናል!0 Comments 0 Shares -
#ETHIOPIA የአመቱ ምርጡ ኮንሰርት "ሀገሬ" !
- - -
የሀገሬ ኮንሰርት ትኬቶችን በቅድሚያ ገዝተው ለሚወዱት በማበርከት ከተወዳጅ አርቲስቶች ጋር አስደሳችና የማይረሳ ምሽት ያሳልፉ
--
የቅድመ ሽያጭ ትኬቶችን በ 251- 904101010 /251- 903101010
-
ቅዳሜ ሚያዝያ 28, 2009 በግዮን ሆቴል እንገናኝ!#ETHIOPIA የአመቱ ምርጡ ኮንሰርት "ሀገሬ" ! - - - የሀገሬ ኮንሰርት ትኬቶችን በቅድሚያ ገዝተው ለሚወዱት በማበርከት ከተወዳጅ አርቲስቶች ጋር አስደሳችና የማይረሳ ምሽት ያሳልፉ -- የቅድመ ሽያጭ ትኬቶችን በ 251- 904101010 /251- 903101010 - ቅዳሜ ሚያዝያ 28, 2009 በግዮን ሆቴል እንገናኝ!0 Comments 0 Shares -
-
-
-
በቅርብ የተቀጠርኩበት ቢሮ ውስጥ!
(አሳዬ ደርቤ)
ከአንድ ወንድና ከአንዲት ሴት የስራ ባልደረባዎቼ ጋር ያለ ስራ ተቀምጨ ሳስተውላቸው እውላለሁ፡፡
ወንዱ ስልጣን ይፈልጋል፡፡ ሴቲቱ ደግሞ ባለ-ስልጣን፡፡ አካሄዳቸው ቢለያይም አላማቸው አንድ ነው፡፡ መንገስ!
ከኮምፒውተራችን ላይ ቀና ብለን ዐይናችን ወደ ልጅዬው ጠረጴዛ ስንልከው ከባጁ ጎን ‹‹ትናንት ምን ሰራሁ? ዛሬ ምን ልስራ? ለነገስ ምን አቀድኩ?›› የሚል ደረቅ ጥያቄ በነጭ ወረቀት ላይ በትልቁ ለጥፎልን እናገኘዋለን፡፡
የለጠፈውን ነገር ከማንበብ አልፈን ‹‹እስኪ የእለቱን ቀርቶ የአመቱን እቅድህን አምጣ?›› ስንለው ግን… የወረቀት ክምር ሲንድ ይቆይና… ዐይኑን ሌላ ቦታ ላይ አስቀምጦ ‹‹እቅድ እንኳን የለኝም›› የሚል መልስ ይሰጠናል፡፡
እይታችንን ከልጁ ላይ አንስተን ወደ ሴቷ መቀመጫ ስንሰደው ጠረጴዛና ወንበሯን እንጂ ልጂቱን አናገኛትም፡፡ ከአንዱ ሚኒስቴር ዲኤታ ወይም ደግሞ ከአንዱ ዳይሬክተር ቢሮ ሄዳለች ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ኮረዳዋ ወፍራም ጭኗቿንና ድቡልቡል ጡቷቿን፣ አስጎብኝታ እስክትመጣ ድረስ ቅኝታችንን ወደ ልጁ ስንመልስ ከጀርባው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴራችንን ፎቶ በትልቁ ለጥፎ… ከፊት ለፊቱ በግራና በቀኝ ሁለት ባንድራዎች ሰክቶ… ወንበሩ ላይ ተጎልቶና አዲስ ራዕይ መጽሔት ላይ ተደፍቶ ጭንቅላቱን በግርምት እየወዘወዘ እናገኘዋለን፡፡
ይሄ ልጅ ሰውን የሚመለከተው በዐይኑ ሳይሆን በግንባሩ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ እንደ እኔ አይነቱን የአስመሳይነት ጥበቡን የባነነበት ሰው ሲያጋጥመው ሰውዬውን የሚያየው እንደ በሬ ከማንጅራቱ ወደ ታች ተቀልብሶ በመሆኑ… ‹‹እዚህ ልጅ ጭንቅላት ላይ የተቀመጠው ኮፊያ ቢነሳ ጸጉሩ መሃከል… ሰውን ለመውጋት ያቆጠቆጡ ‹ቡቃያ ቀንዶች› አይጠፉም!›› ብለን ብናስብ ሐጢያት አይሆንብንም፡፡
‹ልጁ› የአሁን ዘመን ስልጣን ከበረሃ ወጥታ መድረክ ላይ እንደተሰየመች ጠንቅቆ የተረዳ ነው፡፡ ስለዚህ እያንዳንዷን መድረክ ሳይጠቀምባት እንዲታልፈው አይፈልግም፡፡
ለምሳሌ ባለፈው የጥልቅ ተሃድሶ ስብሰባ ያደረግን ጊዜ የመጀመሪያው ተናጋሪ እሱ ነበረ፡፡ በቀረበው ሰነድ ላይ ተመስርቶ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከሊበራል ዲሞክራሲና ከሶሻል ዲሞክራሲ የሚልቅበትን ሁኔታዎች ያስረዳል ተብሎ ሲጠበቅ የማይክራፎኑን ጫፍ እንደ ልጃገረድ ጡት በፍቅር እየደባበሰ ‹ለተሰጠኝ እድል አመሰግናለሁ› እያለ አስር ጊዜ መደጋገሙን ስንሰማ… መድረኩን የሚመሩት ሚኒስቴር ለልጁ የሰጡት ‹‹የአርባ ቀን እድሉን›› እንጂ ‹‹ማይክራፎኑን›› አይመስለንም፡፡
ከዚያ በኋላ ብዙ ትንታኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ ምንም ጭብጥ ያለው ነገር ሳይናገር ‹‹በሕይወቴ እንደዚህ ያለ ጣፋጭ የመወያያ ሰነድ እና ጣፋጭ የሆነ መንግስት አጋጥሞኝ አያውቅም›› ብሎ ሃሳቡን አበቃ፡፡ (ከዚህም ጋር ተያይዞ አንዳንድ ተሰብሳቢዎች ‹‹በህይወቱ ስንት መንግስት እንዳሳለፈ ቢያብራራልን ጥሩ ነበር›› በማለት አንሾካሾኩ!)
.
.
ልጂቱ ከንፈሯን በቀይ ቀለም አፍክታ፣ ማስቲካዋን አፈንድታ ወደ ቢሮ ስለተመለሰች ይሄን አሰልች ሰውዬ ወንበሩ ላይ በተወዘፈበት ትተነው ወደ ኮረዳዋ እንለፍ፡፡
ስሟን ላስተዋውቃሁ መሰል! ‹‹ዘመናይ ትባላለች››
ያ ‹የHip hop› የሙዚቃ ስልትን ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባህር-ዛፍ ፍሬ በጫማው አድርጎ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ያስተዋወቀው ዘፋኝ ማን ነበር? ይሄ እንኳን…..
ዘመናይ ናት እሷ…. ኧኸ
ዘመናይ ናት እሷ…. ኧኸ
ጫማዋ ጥልፍልፍ… ኧኸ
አጭር ነው ቀሚሷ… ኧኸ
ብሎ የዘፈነው…. ኧኸ
ይመስለኛል ለእሷ!..ኧኸ…… ብለን በግጥም ሃሳባችንን እንግለጽና ዘመናይን ከግርጌ ጀምረን እያየናት ወደ ራስጌዋ እንዝለቅ፡፡
ዓመቱን ሙሉ ለጸሐይና ለንፋስ ተጋልጦ የሚኖረው እግሯን ስንመለከት በዐይናችን የሚገባው ቅላቱና ጥራቱ ብቻ ሳይሆን የኮባ ግንድ የመሰለው ልስላሴውም ጭምር ነው፡፡
(አንዳንዴ ባለትዳር ባልሆን ኖሮ አራት ኪሎ ለመግባት ሳይሆን ከዘመናይ ባት ውስጥ ለመግባት ስል ባለስልጣን መሆንን እመኛለሁ፡፡)
ከእግሯ ከፍ ብለን ወደ መቀመጫዋ ስንዘልቅ ‹‹እንስራሽን ባደረገኝ›› ብሎ ያንጎራጎረው ብላቴና ዘፋኝ ይታወሰናል፡፡ እስኪ እንደው በሞቴ አሁን ካልጠፋ ቃላትና ካልጠፋ ምኞት ‹‹ከጀርባሽ እንዲውል እንስራሽን ልሁን›› ብሎ መመኘት ምን ይሉታል? ከዚህ ይልቅ ባንድ ፊቱ ‹ቂጥሽን ባ’ረገኝ› ብሎ ማጠቃለል አይሻልም?... (መቼም የፈለገ ነገር ቢሆን ‹ገል› ከመሆን ‹ገላ› መሆን ሳይሻል አይቀርም፡፡)
ባንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ስተን… ወደላይ ከፍ ስንል አዝራር ለመበጠስና ትዳር ለማፍረስ የተፈጠሩ ሁለት መንትያ ጡቶች ዘመናይ ደረት ላይ ተንጠልጥለው እና አብጠው እናገኛለን፡፡ በታላቅ ተመስጦ ውስጥ ሆኜ ለእነዚህ ጡቶች ቤት ብቻ ሳይሆን ማንጅራትንም ጭምር የሚመታ ግጥም ደርድሬ… ከማሻሸቱ ይልቅ መጥባቱ ላይ ትኩረቱን ያደረገውን ‹‹ልጅሽን ባረገኝ›› የሚል ስያሜ የሰጠሁትን ነጠላ ዘፈኔን ‹በናሁ ቴሌቪዥን› ለመልቀቅ ድምፄ የሚጠራበትንና ፒያኖ የማገኝበትን ቀን እየተጠባበኩ እገኛለሁ፡፡
.
አንባቢ ሆይ ከጡቷ ከፍ ብለን ወደ ፊቷ ስንዘልቅ ልክ እንደኛው ሁላ ዘመናይም በግርምት ውስጥ ሆና ስትመለከተን ዐይን ለዐይን እንገጣጠማለን፡፡ ‹‹እንኳን አይተሺኝ እንዲሁም በርግግ፣ በርግግ ይለኛል›› አለ ሰውዬው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ይሄ የስልጣን ጥመኛም በአንክሮ ሲከታተለኝ ቆይቶ ኖሮ ‹‹ምነው እንደ መቀሌ ሰማዕታት ሀውልት በግርምት ፈዘህ አየሃት’ሳ?›› በማለት ይበልጥ ያደናግጠኛል፡፡
እናም… ‹ምራቃችን ድርቅ፣ ላባችን ፍልቅ› ስላለብን ‹‹የዘንድሮ ሙቀት ገደለን…›› እያልን ወደ ውጭ ስንወጣ ሃይለኛ ንፋስ እና ውርጭ ያጋጠመን ቢሆንም… ወደ ቢሮ ተመልሰን ትረካችንን ከመጨረስ ይልቅ በዚያው መሄዱን መረጥን…በቅርብ የተቀጠርኩበት ቢሮ ውስጥ! (አሳዬ ደርቤ) ከአንድ ወንድና ከአንዲት ሴት የስራ ባልደረባዎቼ ጋር ያለ ስራ ተቀምጨ ሳስተውላቸው እውላለሁ፡፡ ወንዱ ስልጣን ይፈልጋል፡፡ ሴቲቱ ደግሞ ባለ-ስልጣን፡፡ አካሄዳቸው ቢለያይም አላማቸው አንድ ነው፡፡ መንገስ! ከኮምፒውተራችን ላይ ቀና ብለን ዐይናችን ወደ ልጅዬው ጠረጴዛ ስንልከው ከባጁ ጎን ‹‹ትናንት ምን ሰራሁ? ዛሬ ምን ልስራ? ለነገስ ምን አቀድኩ?›› የሚል ደረቅ ጥያቄ በነጭ ወረቀት ላይ በትልቁ ለጥፎልን እናገኘዋለን፡፡ የለጠፈውን ነገር ከማንበብ አልፈን ‹‹እስኪ የእለቱን ቀርቶ የአመቱን እቅድህን አምጣ?›› ስንለው ግን… የወረቀት ክምር ሲንድ ይቆይና… ዐይኑን ሌላ ቦታ ላይ አስቀምጦ ‹‹እቅድ እንኳን የለኝም›› የሚል መልስ ይሰጠናል፡፡ እይታችንን ከልጁ ላይ አንስተን ወደ ሴቷ መቀመጫ ስንሰደው ጠረጴዛና ወንበሯን እንጂ ልጂቱን አናገኛትም፡፡ ከአንዱ ሚኒስቴር ዲኤታ ወይም ደግሞ ከአንዱ ዳይሬክተር ቢሮ ሄዳለች ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ኮረዳዋ ወፍራም ጭኗቿንና ድቡልቡል ጡቷቿን፣ አስጎብኝታ እስክትመጣ ድረስ ቅኝታችንን ወደ ልጁ ስንመልስ ከጀርባው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴራችንን ፎቶ በትልቁ ለጥፎ… ከፊት ለፊቱ በግራና በቀኝ ሁለት ባንድራዎች ሰክቶ… ወንበሩ ላይ ተጎልቶና አዲስ ራዕይ መጽሔት ላይ ተደፍቶ ጭንቅላቱን በግርምት እየወዘወዘ እናገኘዋለን፡፡ ይሄ ልጅ ሰውን የሚመለከተው በዐይኑ ሳይሆን በግንባሩ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ እንደ እኔ አይነቱን የአስመሳይነት ጥበቡን የባነነበት ሰው ሲያጋጥመው ሰውዬውን የሚያየው እንደ በሬ ከማንጅራቱ ወደ ታች ተቀልብሶ በመሆኑ… ‹‹እዚህ ልጅ ጭንቅላት ላይ የተቀመጠው ኮፊያ ቢነሳ ጸጉሩ መሃከል… ሰውን ለመውጋት ያቆጠቆጡ ‹ቡቃያ ቀንዶች› አይጠፉም!›› ብለን ብናስብ ሐጢያት አይሆንብንም፡፡ ‹ልጁ› የአሁን ዘመን ስልጣን ከበረሃ ወጥታ መድረክ ላይ እንደተሰየመች ጠንቅቆ የተረዳ ነው፡፡ ስለዚህ እያንዳንዷን መድረክ ሳይጠቀምባት እንዲታልፈው አይፈልግም፡፡ ለምሳሌ ባለፈው የጥልቅ ተሃድሶ ስብሰባ ያደረግን ጊዜ የመጀመሪያው ተናጋሪ እሱ ነበረ፡፡ በቀረበው ሰነድ ላይ ተመስርቶ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከሊበራል ዲሞክራሲና ከሶሻል ዲሞክራሲ የሚልቅበትን ሁኔታዎች ያስረዳል ተብሎ ሲጠበቅ የማይክራፎኑን ጫፍ እንደ ልጃገረድ ጡት በፍቅር እየደባበሰ ‹ለተሰጠኝ እድል አመሰግናለሁ› እያለ አስር ጊዜ መደጋገሙን ስንሰማ… መድረኩን የሚመሩት ሚኒስቴር ለልጁ የሰጡት ‹‹የአርባ ቀን እድሉን›› እንጂ ‹‹ማይክራፎኑን›› አይመስለንም፡፡ ከዚያ በኋላ ብዙ ትንታኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ ምንም ጭብጥ ያለው ነገር ሳይናገር ‹‹በሕይወቴ እንደዚህ ያለ ጣፋጭ የመወያያ ሰነድ እና ጣፋጭ የሆነ መንግስት አጋጥሞኝ አያውቅም›› ብሎ ሃሳቡን አበቃ፡፡ (ከዚህም ጋር ተያይዞ አንዳንድ ተሰብሳቢዎች ‹‹በህይወቱ ስንት መንግስት እንዳሳለፈ ቢያብራራልን ጥሩ ነበር›› በማለት አንሾካሾኩ!) . . ልጂቱ ከንፈሯን በቀይ ቀለም አፍክታ፣ ማስቲካዋን አፈንድታ ወደ ቢሮ ስለተመለሰች ይሄን አሰልች ሰውዬ ወንበሩ ላይ በተወዘፈበት ትተነው ወደ ኮረዳዋ እንለፍ፡፡ ስሟን ላስተዋውቃሁ መሰል! ‹‹ዘመናይ ትባላለች›› ያ ‹የHip hop› የሙዚቃ ስልትን ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባህር-ዛፍ ፍሬ በጫማው አድርጎ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ያስተዋወቀው ዘፋኝ ማን ነበር? ይሄ እንኳን….. ዘመናይ ናት እሷ…. ኧኸ ዘመናይ ናት እሷ…. ኧኸ ጫማዋ ጥልፍልፍ… ኧኸ አጭር ነው ቀሚሷ… ኧኸ ብሎ የዘፈነው…. ኧኸ ይመስለኛል ለእሷ!..ኧኸ…… ብለን በግጥም ሃሳባችንን እንግለጽና ዘመናይን ከግርጌ ጀምረን እያየናት ወደ ራስጌዋ እንዝለቅ፡፡ ዓመቱን ሙሉ ለጸሐይና ለንፋስ ተጋልጦ የሚኖረው እግሯን ስንመለከት በዐይናችን የሚገባው ቅላቱና ጥራቱ ብቻ ሳይሆን የኮባ ግንድ የመሰለው ልስላሴውም ጭምር ነው፡፡ (አንዳንዴ ባለትዳር ባልሆን ኖሮ አራት ኪሎ ለመግባት ሳይሆን ከዘመናይ ባት ውስጥ ለመግባት ስል ባለስልጣን መሆንን እመኛለሁ፡፡) ከእግሯ ከፍ ብለን ወደ መቀመጫዋ ስንዘልቅ ‹‹እንስራሽን ባደረገኝ›› ብሎ ያንጎራጎረው ብላቴና ዘፋኝ ይታወሰናል፡፡ እስኪ እንደው በሞቴ አሁን ካልጠፋ ቃላትና ካልጠፋ ምኞት ‹‹ከጀርባሽ እንዲውል እንስራሽን ልሁን›› ብሎ መመኘት ምን ይሉታል? ከዚህ ይልቅ ባንድ ፊቱ ‹ቂጥሽን ባ’ረገኝ› ብሎ ማጠቃለል አይሻልም?... (መቼም የፈለገ ነገር ቢሆን ‹ገል› ከመሆን ‹ገላ› መሆን ሳይሻል አይቀርም፡፡) ባንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ስተን… ወደላይ ከፍ ስንል አዝራር ለመበጠስና ትዳር ለማፍረስ የተፈጠሩ ሁለት መንትያ ጡቶች ዘመናይ ደረት ላይ ተንጠልጥለው እና አብጠው እናገኛለን፡፡ በታላቅ ተመስጦ ውስጥ ሆኜ ለእነዚህ ጡቶች ቤት ብቻ ሳይሆን ማንጅራትንም ጭምር የሚመታ ግጥም ደርድሬ… ከማሻሸቱ ይልቅ መጥባቱ ላይ ትኩረቱን ያደረገውን ‹‹ልጅሽን ባረገኝ›› የሚል ስያሜ የሰጠሁትን ነጠላ ዘፈኔን ‹በናሁ ቴሌቪዥን› ለመልቀቅ ድምፄ የሚጠራበትንና ፒያኖ የማገኝበትን ቀን እየተጠባበኩ እገኛለሁ፡፡ . አንባቢ ሆይ ከጡቷ ከፍ ብለን ወደ ፊቷ ስንዘልቅ ልክ እንደኛው ሁላ ዘመናይም በግርምት ውስጥ ሆና ስትመለከተን ዐይን ለዐይን እንገጣጠማለን፡፡ ‹‹እንኳን አይተሺኝ እንዲሁም በርግግ፣ በርግግ ይለኛል›› አለ ሰውዬው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ይሄ የስልጣን ጥመኛም በአንክሮ ሲከታተለኝ ቆይቶ ኖሮ ‹‹ምነው እንደ መቀሌ ሰማዕታት ሀውልት በግርምት ፈዘህ አየሃት’ሳ?›› በማለት ይበልጥ ያደናግጠኛል፡፡ እናም… ‹ምራቃችን ድርቅ፣ ላባችን ፍልቅ› ስላለብን ‹‹የዘንድሮ ሙቀት ገደለን…›› እያልን ወደ ውጭ ስንወጣ ሃይለኛ ንፋስ እና ውርጭ ያጋጠመን ቢሆንም… ወደ ቢሮ ተመልሰን ትረካችንን ከመጨረስ ይልቅ በዚያው መሄዱን መረጥን…0 Comments 0 Shares -
በረኪናው
(አሳዬ ደርቤ)
እንዴት ከረማችሁልኝ? ሰሞኑን ትንሽ ችግር ብጤ አጋጥሞኝ ከፌስቡክ ጠፍቼ ከረምኩ፡፡ ጉዳዩ እንዲህ ነው፡፡
ከወራት በፊት አንድ ጓደኛዬ በስልኬ ደውሎ ለጥብቅ ጉዳይ እንደሚፈልገኝ ስለነገረኝ ስከንፍ ወደ ተቃጠርነበት ቦታ አመራሁ፡፡ ስፍራው ስደርስ ጓደኛዬ ቀድሞኝ ደርሶ አገኘሁት፡፡ ሰውነቱን ስታዘበው አካሉ ከሞጎሳቆሉም በላይ ጺሙ አድጓል፡፡
‹‹ለምን ፈልገኸኝ ነው?›› አልኩት የጀበና ቡናዬን እየተጎነጨሁ፡፡
የያዘውን ጥራዝ ወረቀት አቀበለኝ፡፡ የጥራዙ ሽፋን ላይ ‹‹የፈሳሽ ሳሙና (በረኪና) አዘገጃጀት›› የሚል ጽሁፍ በትልቁ ሰፍሮበታል፡፡
‹‹ስለ በረኪና አዘገጃጀት ማወቅ ምን ያደርግልኛል?›› አልኩት፡፡
‹‹ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ተደራጅቼ በረኪና ማምረት ልጀምር ነው!›› አለኝ፡፡
‹‹አምርታችሁ ምን ልታደርጉት?›› አልኩት ‘ልንጠጣው’ የሚል መልስ እየጠበኩኝ፡፡
‹‹ልንሸጠው!›› በማለት መለሰልኝ፡፡
‹‹ታዲያ ከኔ ምንድን ነው የምትፈልጉት?››
‹‹አብረን እንድንሰራ ነዋ! ፈሳሽ ሳሙና (በረኪና) ለማዘጋጀት የሚስፈልጉ ኬሚካሎችን ለይተን አውቀናቸዋል፡፡ አሁን የሚቀረን ነገር ጥሬ እቃዎቹን አስመጥተን በፋብሪካ እያመረቱ መሸጥ ብቻ ነው፡፡ ይሄን ለማድረግ ደግሞ ትንሽ የካፒታል እጥረት ስላጋጠመን አንድ ተጨማሪ ሰው ማስገባት ግደታ ሆኖብናል! ስለዚህ የኛን ያህል ብር ማዋጣት ከቻልክ አብረን ተጠቃሚ መሆን እንችላለን›› እያለ ማብራራቱን ቀጠለ፡፡
የተሰጠኝ ስብከት ከልጁ ኬሚካል ኢንጅነርነት ጋር ተዳምሮ አፍታም ሳልቆይ ወደ ህልም ውስጥ መግባት ጀመርኩኝ፡፡
.
በቅዠቴ መሃከል ይሄን ስብሰባ የሚበዛበትን ስራዬን ስለቀው ይታየኛል፡፡
በቅዠቴ መሃከል ሙሉአለም በእኛ በረኪና ጋቢዋን ስታቸፈችፍ፣ ሰራዊት ፍቅሬ ‹‹የISO ሁለት ሽ ስምንት ማረጋገጫ ያለው›› እያለ ጋቢውን ጠምዝዞ ሲያሰጣ በቴሌቪዥን ይታየኛል፡፡
በቅዠቴ መሃከል የኛን ብራንድ የተነቀሰች መኪና በረኪናችንን ጭና እንደ አምቡላንስ እየጮኸች ጓዳናውን ስትራወጥበት ይታየኛል፡፡
.
በማግስቱ የሚጠበቅብኝን ገንዘብ እቦታው ድረስ ወስጀ አስረከብኩት፡፡
በረኪና ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉ ኬሚካሎች እና ጥሬ እቃዎች ከየአገሩ እየተፈለጉ ተገዙ፡፡ ኬሚካል ኢንጅነሩ ገዋን ለብሶ፣ ጓንቱን አጥልቆ፣ መነጽሩን ሰክቶ ውሎና አዳሩን ላብራቶሪ ውስጥ አደረገ፡፡ ሲጃራ ሊያጨስና ምግብ ሊቀማምስ ከላብራቶሪ ሲወጣ እንኳን በአንድ እጁ እስኪብርቶ ጨብጦ ፎርሙላ በመደርደርና ፎርሙላ በመናድ ይጠመዳል፡፡
እዚህ ላይ ለሀገራችን ብዙ ምርምሮችን ያደረገው የበእውቱ ስዩም አያት ትዝ አለኝ፡፡ በእውቄ ይሄ ተማራማሪ አያቱ ከአንስታይን ጋር የሚጋራቸውን ባህሪዎች ሲዘረዝር እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹አንስታይን በምርምር ተጠምዶ ሲውል ምሳ መብላቱን ይረሳ ነበር፡፡ የኔም አያት በምርምር ሲጠመድ የበላውን ምሳ እየረሳ ሁለተኛ አምጡ ማለት ጀመረ!›› በማለት የተናገራት ስላቅ ታወሰችኝ፡፡
የእኔው ተመራማሪ ደግሞ በጀመረው ሂሳብ ላይ ከመመሰጡ የተነሳ የለኮሰው ሲጋራ ነዶ አልቆ፣ ጣቱን ሲያቃጥለው እንኳን አይሰማውም ነበር፡፡ እኛ ስለ በረኪናው እንጂ ስለ ፎርሙላው ሃሳቡ የሌለን ጓደኞቹ ‹‹ዩራኒየም ከማብላላት በረኪና ማብላላት በጣም እውቀትን ይጠይቃል›› የሚል መደምደሚ ላይ ደረስን፡፡
.
የተጠመቀው በረኪና የላብራቶሪ ሂደቱም ጨርሶ የሚሞከርበት ቀን ደረሰ፡፡ ፈሳሽ ሳሙናው በጠርሙስ ውስጥ ሲታይ መልኩም ሆነ ውፍረቱ ነጭ ወለላ ማር ይመስላል፡፡ ውሃ የያዘ ሳፋ ላይ ጠብታ በረኪና ተጨመረ፡፡ ወጥ እና ላብ ያቆሸሸው የተመራማሪያችን ገዋን በዚህ ታምረኛ ሳሙና ሊታጠብ ወደ ሳፋው ውስጥ ገባ፡፡
ልብስ አጣቢዋ (ላብ ቴክኒሽያኗ) በረኪናውን እንድኳርፍ ለማድረግ በጉራጌኛ ውዝዋዜ መዳፎቿን አሾረቻቸው፡፡ ግንባሯ ላይ ላቧ እስኪፈልቅ ድረስ ብትታገልም ወፍ እና መኳረፍ የሚባል ነገር ሳይታይ ቀረ፡፡
‹‹እስኪ በረኪናውን በደንብ አድርግበት›› አለው ከባለሀብቶቹ መሃከል አንዱ፡፡
የውሃው ቀለም እስኪለወጥ ዝርግፍ አድርጎ ጨመረበት፡፡
የማይኳርፍ በረኪና እና ያኮረፉ ፊቷች ላብራቶሪው ውስጥ ነገሱ፡፡ ሳፋው ውስጥ ሊታጠብ የገባው ገዋን የመቆሸሽ ሁኔታ ተስተዋለበት፡፡ ገዋኑን ለማንጻት የእኛን በረኪና የሚያስለቅቅ ሌላ በረኪና አስፈለገ፡፡ አንዱ ሸሪካችን ‹‹እንዴት ያን ሁሉ ገንዘብ ጨፍጭፈን በበረኪና ፈንታ ቆሻሻ ልናመርት ቻልን?›› በማለት ገዋኑን አንስቶ ወረወረው፡፡
.
አሁን የተመራማሪነቱን ሚና እኔ ወስጃለሁ፡፡ ከላብራቶሪው እየሮጥኩኝ በመውጣት ሜሪንዳና ወተት ይዠ ተመለስኩ፡፡
‹‹ምን ልታደርግ ነው?›› አሉኝ፡፡
‹‹እዚህ ሀገር በበረኪና ከሚያጥበው ይልቅ በረኪና የሚጠጣው ይበዛል! ስለዚህ የእኛ በረኪና እጥበቱ አርኪ ባይሆንም መርዘኝነቱ የተሻለ ሊሆን ይችላል! ይሄን ደግሞ እኔ ልሞክረው ወስኛለሁ! እናም በረኪናውን ጠጥቼ የመዝለፍለፍ ሁኔታ ካስተዋላችሁብኝ ወተቱን፣ ምንም ለውጥ ካልተከሰተ ደግሞ ሜሪንዳውን እንድትግቱኝ!›› በማለት ተናዘዝኩኝ፡፡ (ጊዜው የእኔ ተስፋ የተሟጠጠበት እና የሜሪንዳ ስም የጠፋበት ስለነበር፣ በረኪናው ለልብስ እጠበትም፣ ለነፍስ ማጥፋትም የማይሆን ከሆነ ሜሪንዳውን ጠጥቼ ይችን ምድር ለመሰናበት ወስኛለሁ፡፡)
በረኪና የያዘውን ጠርሙስ አነሳሁና ‹‹ዥው›› አድርጌ ጠጣሁት፡፡
እራሴን እንዲያዞረኝ፣ ሆዴን እንድያጥወለውለኝ ጾለት አደረስኩኝ፡፡ ጉልበቴ ተዳክ፣ ዐይኔ ተስለምልሞ ማየት ፈለኩኝ፡፡
ከግሳት ውጭ ምንም የተከሰተ ነገር አልነበረም፡፡ ‹‹ከዚህ በላይ መኖር መዋጮ ለመጠየቅ ነው›› አልኩና ሚሪንዳውን በማንሳት ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት፡፡
የተዳከመ መንፈሴ ሲነቃቃ፣ በንደት የተቃጠለ ጨጓራየ ሲቀዘቅዝ ተሰማኝ፡፡
የላብራቶሪውን ጠረጴዛ በቡጢ ስጠልዘው እንክትክቱ ወጣ፡፡
እንዴ!! ይሄን ሁሉ ሃይል ከየት አመጣሁት?
ምናልባት የነ ‹‹ገንዘቤ›› አሰልጣኝ ሻንጣው ውስጥ የተገኘበት አበረታች መድሃኒት ይሄ ይሆን እንዴ?
ይሄን ለመመለስ ተጨማሪ ጊዜ እና ተጨማሪ ምርምር ይጠይቃል፡፡
እስከዚያው ግን ሰላም እደሩልኝ!በረኪናው (አሳዬ ደርቤ) እንዴት ከረማችሁልኝ? ሰሞኑን ትንሽ ችግር ብጤ አጋጥሞኝ ከፌስቡክ ጠፍቼ ከረምኩ፡፡ ጉዳዩ እንዲህ ነው፡፡ ከወራት በፊት አንድ ጓደኛዬ በስልኬ ደውሎ ለጥብቅ ጉዳይ እንደሚፈልገኝ ስለነገረኝ ስከንፍ ወደ ተቃጠርነበት ቦታ አመራሁ፡፡ ስፍራው ስደርስ ጓደኛዬ ቀድሞኝ ደርሶ አገኘሁት፡፡ ሰውነቱን ስታዘበው አካሉ ከሞጎሳቆሉም በላይ ጺሙ አድጓል፡፡ ‹‹ለምን ፈልገኸኝ ነው?›› አልኩት የጀበና ቡናዬን እየተጎነጨሁ፡፡ የያዘውን ጥራዝ ወረቀት አቀበለኝ፡፡ የጥራዙ ሽፋን ላይ ‹‹የፈሳሽ ሳሙና (በረኪና) አዘገጃጀት›› የሚል ጽሁፍ በትልቁ ሰፍሮበታል፡፡ ‹‹ስለ በረኪና አዘገጃጀት ማወቅ ምን ያደርግልኛል?›› አልኩት፡፡ ‹‹ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ተደራጅቼ በረኪና ማምረት ልጀምር ነው!›› አለኝ፡፡ ‹‹አምርታችሁ ምን ልታደርጉት?›› አልኩት ‘ልንጠጣው’ የሚል መልስ እየጠበኩኝ፡፡ ‹‹ልንሸጠው!›› በማለት መለሰልኝ፡፡ ‹‹ታዲያ ከኔ ምንድን ነው የምትፈልጉት?›› ‹‹አብረን እንድንሰራ ነዋ! ፈሳሽ ሳሙና (በረኪና) ለማዘጋጀት የሚስፈልጉ ኬሚካሎችን ለይተን አውቀናቸዋል፡፡ አሁን የሚቀረን ነገር ጥሬ እቃዎቹን አስመጥተን በፋብሪካ እያመረቱ መሸጥ ብቻ ነው፡፡ ይሄን ለማድረግ ደግሞ ትንሽ የካፒታል እጥረት ስላጋጠመን አንድ ተጨማሪ ሰው ማስገባት ግደታ ሆኖብናል! ስለዚህ የኛን ያህል ብር ማዋጣት ከቻልክ አብረን ተጠቃሚ መሆን እንችላለን›› እያለ ማብራራቱን ቀጠለ፡፡ የተሰጠኝ ስብከት ከልጁ ኬሚካል ኢንጅነርነት ጋር ተዳምሮ አፍታም ሳልቆይ ወደ ህልም ውስጥ መግባት ጀመርኩኝ፡፡ . በቅዠቴ መሃከል ይሄን ስብሰባ የሚበዛበትን ስራዬን ስለቀው ይታየኛል፡፡ በቅዠቴ መሃከል ሙሉአለም በእኛ በረኪና ጋቢዋን ስታቸፈችፍ፣ ሰራዊት ፍቅሬ ‹‹የISO ሁለት ሽ ስምንት ማረጋገጫ ያለው›› እያለ ጋቢውን ጠምዝዞ ሲያሰጣ በቴሌቪዥን ይታየኛል፡፡ በቅዠቴ መሃከል የኛን ብራንድ የተነቀሰች መኪና በረኪናችንን ጭና እንደ አምቡላንስ እየጮኸች ጓዳናውን ስትራወጥበት ይታየኛል፡፡ . በማግስቱ የሚጠበቅብኝን ገንዘብ እቦታው ድረስ ወስጀ አስረከብኩት፡፡ በረኪና ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉ ኬሚካሎች እና ጥሬ እቃዎች ከየአገሩ እየተፈለጉ ተገዙ፡፡ ኬሚካል ኢንጅነሩ ገዋን ለብሶ፣ ጓንቱን አጥልቆ፣ መነጽሩን ሰክቶ ውሎና አዳሩን ላብራቶሪ ውስጥ አደረገ፡፡ ሲጃራ ሊያጨስና ምግብ ሊቀማምስ ከላብራቶሪ ሲወጣ እንኳን በአንድ እጁ እስኪብርቶ ጨብጦ ፎርሙላ በመደርደርና ፎርሙላ በመናድ ይጠመዳል፡፡ እዚህ ላይ ለሀገራችን ብዙ ምርምሮችን ያደረገው የበእውቱ ስዩም አያት ትዝ አለኝ፡፡ በእውቄ ይሄ ተማራማሪ አያቱ ከአንስታይን ጋር የሚጋራቸውን ባህሪዎች ሲዘረዝር እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹አንስታይን በምርምር ተጠምዶ ሲውል ምሳ መብላቱን ይረሳ ነበር፡፡ የኔም አያት በምርምር ሲጠመድ የበላውን ምሳ እየረሳ ሁለተኛ አምጡ ማለት ጀመረ!›› በማለት የተናገራት ስላቅ ታወሰችኝ፡፡ የእኔው ተመራማሪ ደግሞ በጀመረው ሂሳብ ላይ ከመመሰጡ የተነሳ የለኮሰው ሲጋራ ነዶ አልቆ፣ ጣቱን ሲያቃጥለው እንኳን አይሰማውም ነበር፡፡ እኛ ስለ በረኪናው እንጂ ስለ ፎርሙላው ሃሳቡ የሌለን ጓደኞቹ ‹‹ዩራኒየም ከማብላላት በረኪና ማብላላት በጣም እውቀትን ይጠይቃል›› የሚል መደምደሚ ላይ ደረስን፡፡ . የተጠመቀው በረኪና የላብራቶሪ ሂደቱም ጨርሶ የሚሞከርበት ቀን ደረሰ፡፡ ፈሳሽ ሳሙናው በጠርሙስ ውስጥ ሲታይ መልኩም ሆነ ውፍረቱ ነጭ ወለላ ማር ይመስላል፡፡ ውሃ የያዘ ሳፋ ላይ ጠብታ በረኪና ተጨመረ፡፡ ወጥ እና ላብ ያቆሸሸው የተመራማሪያችን ገዋን በዚህ ታምረኛ ሳሙና ሊታጠብ ወደ ሳፋው ውስጥ ገባ፡፡ ልብስ አጣቢዋ (ላብ ቴክኒሽያኗ) በረኪናውን እንድኳርፍ ለማድረግ በጉራጌኛ ውዝዋዜ መዳፎቿን አሾረቻቸው፡፡ ግንባሯ ላይ ላቧ እስኪፈልቅ ድረስ ብትታገልም ወፍ እና መኳረፍ የሚባል ነገር ሳይታይ ቀረ፡፡ ‹‹እስኪ በረኪናውን በደንብ አድርግበት›› አለው ከባለሀብቶቹ መሃከል አንዱ፡፡ የውሃው ቀለም እስኪለወጥ ዝርግፍ አድርጎ ጨመረበት፡፡ የማይኳርፍ በረኪና እና ያኮረፉ ፊቷች ላብራቶሪው ውስጥ ነገሱ፡፡ ሳፋው ውስጥ ሊታጠብ የገባው ገዋን የመቆሸሽ ሁኔታ ተስተዋለበት፡፡ ገዋኑን ለማንጻት የእኛን በረኪና የሚያስለቅቅ ሌላ በረኪና አስፈለገ፡፡ አንዱ ሸሪካችን ‹‹እንዴት ያን ሁሉ ገንዘብ ጨፍጭፈን በበረኪና ፈንታ ቆሻሻ ልናመርት ቻልን?›› በማለት ገዋኑን አንስቶ ወረወረው፡፡ . አሁን የተመራማሪነቱን ሚና እኔ ወስጃለሁ፡፡ ከላብራቶሪው እየሮጥኩኝ በመውጣት ሜሪንዳና ወተት ይዠ ተመለስኩ፡፡ ‹‹ምን ልታደርግ ነው?›› አሉኝ፡፡ ‹‹እዚህ ሀገር በበረኪና ከሚያጥበው ይልቅ በረኪና የሚጠጣው ይበዛል! ስለዚህ የእኛ በረኪና እጥበቱ አርኪ ባይሆንም መርዘኝነቱ የተሻለ ሊሆን ይችላል! ይሄን ደግሞ እኔ ልሞክረው ወስኛለሁ! እናም በረኪናውን ጠጥቼ የመዝለፍለፍ ሁኔታ ካስተዋላችሁብኝ ወተቱን፣ ምንም ለውጥ ካልተከሰተ ደግሞ ሜሪንዳውን እንድትግቱኝ!›› በማለት ተናዘዝኩኝ፡፡ (ጊዜው የእኔ ተስፋ የተሟጠጠበት እና የሜሪንዳ ስም የጠፋበት ስለነበር፣ በረኪናው ለልብስ እጠበትም፣ ለነፍስ ማጥፋትም የማይሆን ከሆነ ሜሪንዳውን ጠጥቼ ይችን ምድር ለመሰናበት ወስኛለሁ፡፡) በረኪና የያዘውን ጠርሙስ አነሳሁና ‹‹ዥው›› አድርጌ ጠጣሁት፡፡ እራሴን እንዲያዞረኝ፣ ሆዴን እንድያጥወለውለኝ ጾለት አደረስኩኝ፡፡ ጉልበቴ ተዳክ፣ ዐይኔ ተስለምልሞ ማየት ፈለኩኝ፡፡ ከግሳት ውጭ ምንም የተከሰተ ነገር አልነበረም፡፡ ‹‹ከዚህ በላይ መኖር መዋጮ ለመጠየቅ ነው›› አልኩና ሚሪንዳውን በማንሳት ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት፡፡ የተዳከመ መንፈሴ ሲነቃቃ፣ በንደት የተቃጠለ ጨጓራየ ሲቀዘቅዝ ተሰማኝ፡፡ የላብራቶሪውን ጠረጴዛ በቡጢ ስጠልዘው እንክትክቱ ወጣ፡፡ እንዴ!! ይሄን ሁሉ ሃይል ከየት አመጣሁት? ምናልባት የነ ‹‹ገንዘቤ›› አሰልጣኝ ሻንጣው ውስጥ የተገኘበት አበረታች መድሃኒት ይሄ ይሆን እንዴ? ይሄን ለመመለስ ተጨማሪ ጊዜ እና ተጨማሪ ምርምር ይጠይቃል፡፡ እስከዚያው ግን ሰላም እደሩልኝ!0 Comments 0 Shares