0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበኦሮሚያ ክልል በርካታ ዞኖች በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች በወባ ተይዘዋልበኦሮሚያ ክልል በሚገኙ በርካታ ዞኖች፣ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸውን፣ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በከፍተኛ ደረጃ ከተጠቁት ዞኖች አንዱ በኾነው በምዕራብ ወለጋ ዞን ብቻ፣ ባለፉት ዐሥር ወራት ውስጥ፣ ከ500ሺሕ በላይ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን፣ የዞኑ የጤና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መስፍን ጣሰው ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል። በዚኹ ዞን የቆንዳላ ወረዳ ነዋሪዎች ደግሞ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ በወባ የሞቱ ሕፃናት መኖራቸውን...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMከጋምቤላ ከተማ ወደ ኑዌር ዞን የትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡ ተገለጸከጋምቤላ ከተማ ወደ ኑዌር ዞን የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ፣ የኑዌር ዞን ተጓዦች ለችግር መዳረጋቸውን ተናገሩ፡፡ የዞኑ ተጓዦች ይጠቀሙበት የነበረው የኒውላንድ መናኸርያ ተዘግቶ፣ ሁሉም ተጓዦች በዋናው መናኸርያ እንዲጠቀሙ በክልሉ መንግሥት መወሰኑን የገለጸው የትራንስፖርት ቢሮው በበኩሉ፣ ኾኖም ኑዌር ተጓዧች በጸጥታ ስጋት ምክንያት በዋናው መናኸርያ ለመገልገል ባለመፈለጋቸው ችግሩ ማጋጠሙን አስታውቋል፡፡ መንግሥት ይህን ውሳኔ ከማሳለፉ በፊት፣ በአኙዋክ እና...0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበናይጄሪያ የምግብ ባንክ ከትርፍ አምራቾች ያከማቸውን እህል ለተቸገሩት እያዳረሰ ነውናይጄሪያ፣ ለዐሥርት ዓመታት ያልታየ የኑሮ ውድነት ቀውስ ገጥሟታል። በያዝነው ዓመት፣ 31 ሚሊዮን የሚኾኑ ናይጄሪያውያን የከፋ ረኀብ እንደሚገጥማቸው፣ ተመድ አስታውቋል። በሌጎስ የሚገኝ አንድ የምግብ ባንክ፣ ከገበሬዎች ጋራ በመተባበር፣ ከትርፍ አምራች አካባቢዎች እህል በመሰብሰብ ላይ ነው። ዓላማውም፣ እህሉ ሳይባክን የምግብ እጥረት ለገጠማቸው ቤተሰቦች እንዲውል ማድረግ ነው። ቲመቲ ኦቢይዙ ከሌጎስ የላከውን ዘገባ እንግዱ ወልዴ ወደ አማርኛ መልሶታል።0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMየከፊል አውቶማቲክ ጠመንጃዎች የቃታ አጠቃቀም እገዳ ተቀለበሰየዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ከፊል አውቶማቲክ ጠመንጃዎች፣ እንደ መትረየስ አከታትለው ጥይት እንዲተኩሱ የሚገጠመው ማቀባበያ ቃታ ጥቅም ላይ እንዳይውል የከለከለውን እገዳ፣ ባለፈው ሳምንት ቀልብሶታል። የአሜሪካ ድምፁ ስካት ስተርንስ ባጠናቀረው ዘገባ እንዳመለከተው፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የመሣሪያ እና የመሣሪያ ባለቤትነት ጉዳይ፣ በመጪው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዐቢይ ጉዳይ ኾኖ እንዲቀጥል ያደርጋል። ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች።0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMአሜሪካዊ ያልኾኑ ሰዎች “ድምፅ ይሰጣሉ” የሚለው ቅሬታ የመራጮች መታወቂያ ሕጎች ጉዳይየሪፐብሊካን ፓርቲው ፕሬዚዳንታዊ እጩ ዶናልድ ትራምፕ፣ ስደተኞችን ጨምሮ አሜሪካዊ ዜግነት የሌላቸው ሰዎች፣ “በሕገ ወጥ መንገድ በዩናይትድ ስቴትስ ምርጫ ድምፅ እየሰጡ ነው፤” ብለዋል። አንድ በካሊፎርኒያ ክፍለ ግዛት ውስጥ የምትገኝ ከተማ፣ የግዛቲቱን የድምፅ አሰጣጥ ሕጎችን የሚጥሱ የመራጭ መታወቂያ ሕጎችን ተፈጻሚ ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምራለች። ጂኒያ ዱላ ያደረሰችንን ዘገባ፣ አሉላ ከበደ ወደ አማርኛ መልሳዋለች።0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበደቡባዊ አፍሪካ 60 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ ዋስትና ችግር እንዳለባቸው ተመድ አመለከተየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ 60 ሚሊዮን የሚደርሱ የደቡባዊ አፍሪካ ሕዝቦች፣ በኤልኒኖ ምክንያት በተፈጠረው ድርቅ ለምግብ ዋስትና ዕጦት መዳረጋቸውን አመልክቷል፡፡ ችግሩ ያለው በማላዊ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ብቻ ሳይኾን፣ ዓለም አቀፍ የርዳታ ጥሪዎችን ባቀረቡ ሀገራትም እንደኾነ ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ ኮሎምበስ ማቭሁንጋ ከዚምባብዌ እንደዘገበው፣ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት፣ ቀውሱን ለማቃለል ተስፋ በማድረግ 10 ሚሊዮን ዶላር እየለቀቀ ነው።0 Comments 0 Shares
-
AMHARIC.VOANEWS.COMሴኔጋል ከ50 ሚሊዮን በላይ የሚገመት ኮኬይን ያዘችየሴኔጋል ጉምሩክ ባለፉት አምስት ቀናት ውስጥ በድምሩ ከ50 ሚሊየን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው ሦስት የኮኬይን ጭነቶች መያዙን ትላንት ማክሰኞ ዕለት አስታወቀ። የጉምሩክ ባለስልጣናት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከአጎራባች ሀገሮች፣ በተለይም በላቲን አሜሪካ እየተመረተ ወደ አውሮፓ የሚጓዘውን አደንዛዥ ዕፅ ማስተላለፊያ ከሆኑት ጊኒ፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ-ቢሳው እና ማሊ የሚገባውን ኮኬይን በብዛት እየያዙ ይገኛሉ። ፖሊስ ትላንት ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ ከማሊ ጋር በሚያዋስነው...0 Comments 0 Shares