• AMHARIC.VOANEWS.COM
    በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ምክትል ፕሬዝዳንትነት
    በአሜሪካ ምርጫ፣ የምክትል ፕሬዚደንትነት ዕጩ ተወዳዳሪዎቹ ጄዲ ቫንስ እና ቲም ዋልዝ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያም የመጨረሻም የሆነ ክርክራቸውን ያከናውናሉ። የአሜሪካ ድምጹ ስካት ስተርንስ ዕጩዎቹ ኒውዮርክ ላይ ሲገናኙ ያነሷቸዋል ተብለው የሚገመቱ ጉዳዮችን ቃኝቷል።
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የአፍሪካ ዲያስፖራዎች ስለ አሜሪካ ምርጫ ምን ይላሉ?
    ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ኻሪስ ወደ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፉክክር ከመግባታቸው በፊት፣ ከዩናይትድ ስቴትስ መራጮች ገሚስ ያህሉ በፕሬዝዳንት ባይደን እና በቀድሞ ፕሬዝዳንት ትረምፕ ደስተኛ እንዳልነበሩ ከህዝብ የተሰበሰቡ አስተያየቶች ያሳያሉ። ያሳለፍነው ሚያዚያ ወር ላይ፣ በዚህ ምርጫ ድምፃቸውን መስጠት እንደማያስቡ የገለጹልን አንድ የአፍሪካ ዲያስፖራ ማኅበረሰብ አባል አነጋግረን የነበረ ሲሆን፣ የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ጄፍ ስዊኮርድ በቅርቡ በድጋሚ አግኝቷቸው፣ የካማላ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የእገታ ወንጀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የአማራ ክልል ፖሊስ አስታወቀ
    በአማራ ክልል፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት እየጨመረ የመጣው በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸም የእገታ ወንጀል ‘ከአሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል’ መድረሱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በኮሚሽኑ የሚዲያ ጉዳዮች ዋና ክፍል ኃላፊ ኮማንደር መሳፍንት እሸቴ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ ባለፈው አመት ብቻ ከ287 በላይ የእገታ ወንጀሎች ተፈፅመዋል። በክልሉ ውስጥ የተፈጠሩ ግጭቶችን ለእገታው ወንጀል መጨመር እንደ ምክንያት ያነሱት፣ ኮማንደር መሳፍንት መረጃው ለፖሊስ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ቴል አቪቭ እና አካባቢው ያለው ሁኔታ
    የመካከለኛው ምሥራቅ ውጥረት ተባብሶ ቀጥሏል፡፡ ኢራን በዛሬው ዕለት ቁጥሩ ወደ 180 የሚጠጋ ሚሳኤል ወደ እስራኤል ተኩሳለች፡፡ ይሁንና በሚሳኤሎቹ ጥቃት እስካሁን የደረሰ ጉዳት አልተዘገበም፡፡ በሌላ በኩል በቴል አቪቭ በተኩስ እና በስለት በተፈፀመ ጥቃት ቢያንስ ስድስት ሰዎች ሲገደሉ ዘጠኝ ደግሞ ቆስለዋል።"ሽብርተኞች" ብሎ በገለጻቸው ሁለት ግለሰቦች ጥቃቱ እንደተፈፀመ የእስራኤል ፖሊስ አስታውቋል። እንዲህ ባለው የሚሳኤል ጥቃት ወቅት እንደሚያደርጉት ሁሉ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ኢራን በርካታ ሚሳዬሎችን ወደ እስራኤል አስወነጨፈች
    ኢራን በርካታ ሚሳዬሎችን ወደ እስራኤል ማስወጨፏን እስራኤል አስታውቃለች፡፡ ነዋሪዎች በቦምብ መጠለያ አካባቢ እንዲሆኑ የእስራኤል ሠራዊት ሲመክር፣ የአደጋ ማስጠንቀቂያ ጥሪ በመላ ሃገሪቱ ተሰምቷል። ኢራን ባሊስቲክ ሚሳዬሎችን በቅርቡ ለማስወንጨፍ በመዘጋጀት ላይ ነች ሲሉ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለሥልጣን አስታውቀው ነበር። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት ባለሥልጣን እንዳሉት፣ ኢራን ጥቃቱን የምትፈጽም ከሆነ “አደገኛ ውጤት” ይኖረዋል። እስራኤል ባለፈው...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    በቱኒዚያ ለፕሬዝደንትነት የሚወዳደሩት ፖለቲከኛ የ12 ዓመት እስር ተፈረደባቸው
    በቱኒዚያ የሚገኝ ፍ/ቤት፣ የተቃዋሚው ፓርቲው ፕሬዝደንታዊ ዕጩ ላይ የ12 ዓመት እስር ቅጣት አስተላልፏል። የድምፅ ሰጪዎችን ይሁንታ በሚያሰባስቡበት ጊዜ ማጭበርበር ፈፅመዋል የተባሉት የተቃዋሚው ዕጩ አያቺ ዛሜል፣ በመጪው እሁድ በሚደረገው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ላይ ተፎካካሪ ሆነው እንደሚቀጥሉ ጠበቃቸው አስታውቀዋል። ውድድሩን በመምራት ላይ ያሉትና አሁን በሥልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝደንት ካይስ ሳያድ በእ.አ.አ 2019 ወደ ሥልጣን የመጡ ሲሆን፣ ፓርላማውን አፍርሰው...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    በአሜሪካ የወደብ ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማ መቱ
    በአሜሪካ የወደብ ሠራተኞች ከክፍያ እና ከሌሎችም ጉዳዮች ጋራ በተያያዘ የሥራ ማቆም አድማ መተዋል። አድማው ከጥቂት ሳምንታት በላይ የሚዘልቅ ከሆነ የዋጋ ግሽበትን እና የሸቀጥ እጥረትን ሊያባብስ ይችላል ተብሏል። 45 ሺሕ ዓባላት ያሉት የወደብ ሠራተኞች ማኅበር አድማ፣ 36 ወደቦች ላይ መስተጓጎል ሊፈጥር እንደሚችል ታውቋል። በወደቦቹ እና በሰራተኞቹ መካከል ያለው ውል ዛሬ ሌሊት ላይ እንዳበቃ ሲታወቅ፣ ድርድሩ መጠነኛ መሻሻል እያሳየ ነው ተብሏል። ከሜይን...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ጂሚ ካርተር 100ኛ ዓመት ልደታቸውን አከበሩ
    የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር 100ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ዛሬ አክብረዋል። በዚህም የመጀመሪያው አንድ መቶ ዓመት ዕድሜ የቆዩ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነዋል። ከእ.አ.አ 1977 እስከ 1981፣ 39ኛው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው ያገለገሉት ጂሚ ካርተር፣ ላለፉት አርባ ዓመታት በላይ ለሚሆን ጊዜ ደግሞ ‘የካርተር ማዕከል’ ለተሰኘውና ከባለቤታቸው ሮዘሊን ካርተር ጋራ በመሆን ለመሠረቱት መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሠርተዋል። ሮዘሊን ካርተር በ96...
    0 Comments 0 Shares